የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የባህር በር የዚህ ትውልድ ብሔራዊ አጀንዳ ነው

Aug 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ)፦ የባህር በር የዚህ ትውልድ ብሔራዊ አጀንዳ መሆኑን የማህበራዊ ሳይንስ ምሁር ብርሀኑ ሌንጂሶ (ዶ/ር) ገለጹ።

ኢትዮጵያ በታሪክም ሆነ ህጋዊ መሰረትን በካደ ሁኔታ ያጣችው የባህር በር ኢኮኖሚያዊ ዕድገቷን እንደጎዳው ምሁራን ያስረዳሉ።

ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤት እንድትሆንና ብሔራዊ ጥቅምን ማስከበር ላይ የተሄደበትን ርቀት አስመልክቶ ኢዜአ ከማህበራዊ ሳይንስ ምሁሩ ብርሀኑ ሌንጂሶ (ዶ/ር ) ጋር ቆይታ አድርጓል።

ምሁሩ በቆይታቸው እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ታሪካዊ፣ ጂኦ-ፖለቲካዊና ህጋዊ መሰረትን የተከተለ ነው።

በውጭ ኃይሎች ሴራና በሀገር ውስጥ በነበሩ ውስብስብ ችግሮች ምክንያት ሀገሪቱ ያጣችውን የባህር በር ባለቤትነት ለማስመለስ የጀመረችው ህጋዊና ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ወቅታዊ መሆኑን ጠቁመዋል።

ዓለም አቀፍ የባህር ህግ ወደብ የሌላቸው ሀገራት ወደ ባህር የመድረስና የመጠቀም መብታቸውን በግልፅ እውቅና ይሰጣል ብለዋል።

ይህም ሀገራት ብሔራዊ ጥቅማቸውን ለማስከበርና የባህር በር ለማግኘት ለሚያደርጉት ዲፕሎማሲያዊና ህጋዊ ጥረት ትልቅ መሰረት ነው ሲሉ አክለዋል።

ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን በሴራ ብታጣም ዳግም የባህር በር ባለቤት ለመሆን የጀመረችው ጥረት የህግና የታሪክ መሰረት ያለው መሆኑን አስረድተዋል።

የባህር በር ጥያቄው የኢትዮጵያን የንግድ ሚዛን ከማስጠበቅ ባሻገር፣ ለአፍሪካ ቀንድ ቀጣና የጋራ ተጠቃሚነትና አስተማማኝ ሰላም የላቀ አስተዋጽኦ እንዳለውም ብርሃኑ (ዶ/ር ) አክለዋል።

ኢትዮጵያ አስተማማኝ የባህር በር ማግኘቷ ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚኖራትን የንግድና የኢኮኖሚ ትስስር በማሳደግ ቀጠናዊ ውህደትን ያፋጥናል ሲሉም ገልጸዋል።

ብርሀኑ ሌንጂሶ (ዶ/ር) የባህር በር የትውልድ ብሔራዊ ህልውና ጉዳይ መሆኑንም ገልጸዋል።

ለተግባራዊነቱም ዜጎች የፖለቲካም ሆነ ሌሎች አመለካከት ልዩነቶቻቸውን ወደ ጎን በመተው ለሀገር ብሔራዊ ጥቅም በጋራ መቆም አለባቸው ብለዋል።

መንግስት በሰላማዊና በዲፕሎማሲያዊ መርህ የጀመረውን ጥረት ለማሳካት የሕዝብ ዲፕሎማሲ ተሳትፎ ሊጠናከር ይገባል ሲሉም አመልክተዋል።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና የዘርፉ ምሁራን የባህር በር ለማግኘት የተጀመረውን ሀገራዊ ጥረት በምርምር፣ በታሪካዊና በህጋዊ ሰነዶች በማስደገፍ ሙያዊ ግዴታቸውን እንዲወጡ መክረዋል።

የኢትዮጵያን ዘላቂ ጥቅም ለማስከበርና የባህር በር ባለቤትነትን እውን ለማድረግ አሁን የተጀመሩት ሁሉን አቀፍ ጥረቶች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ምሁሩ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026

ባለፉት አምስት ዓመታት አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ ተችሏል – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ ባለፉት አምስት ዓመታት ስር የሰደዱ ችግሮችን በመቅረፍ አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ መቻሉን የአዲስ...

Jul 18, 2026

በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገበ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገ...

Jun 24, 2026