የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በአማራ ክልል በመኸር እርሻ 5 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር ተሸፍኗል

Aug 10, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ) ፦በአማራ ክልል በመኸር እርሻ 5 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ።

በቢሮው የሰብል ልማት ማስፋፊያ ባለሙያ ወይዘሮ እንየ አሰፋ እንደገለጹት፤ በተያዘው የክረምት ወቅት የመኸር እርሻ 5 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ ወደ ስራ ተገብቷል።

በዚህም እስካሁን ከ5 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በዘር በመሸፈን የእቅዱን 91 በመቶ ማሳካት ተችሏል ብለዋል።

እቅዱን ሙሉ ለሙሉ ለማሳካትም ጤፍ፣ ሽንብራና ሌሎች ፈጥነው የሚደርሱ ሰብሎችን በመዝራት በአጠቃላይ 205 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማምረት ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

ከዚህ ውስጥ ከ2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም የለማ ሲሆን በመስመር መዝራትና ሌሎች አዳዲስ አሰራሮች መተግበራቸውንም አስረድተዋል።

በተጨማሪም ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችል 2 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል ማዳበሪያ እስካሁን ጥቅም ላይ መዋሉን አረጋግጠዋል።

በደቡብ ጎንደር ዞን ፎገራ ወረዳ ቋር ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ወንድምሁነኝ ዘለቀ እንደገለጹት፤ በክረምቱ አንድ ሄክታር ተኩል መሬታቸውን በሩዝ ሰብል በመሸፈን የመንከባከብ ስራ እየሰሩ ይገኛሉ።

ምርታማነቱን ለማሳደግም 2 ኩንታል ማዳበሪያ ተጠቅመው መዝራታቸውን ጠቁመው፣ ከዘሩት ማሳ ላይ 75 ኩንታል የሩዝ ምርት ለማግኘት እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።

በባህር ዳር ከተማ ዘንዘልማ ቀበሌ ነዋሪው አርሶ አደር ከፍያለው ንጉሴ በበኩላቸው፤ ለመኸር እርሻ አስፈላጊ ግብአቶችን በማግኘታቸው ከ5 ሄክታር በላይ በሆነ መሬታቸው ሩዝ፣ ዳጉሳ፣ ማሽላና ጤፍ ማልማታቸውን ተናግረዋል።

ከዚህም ከ130 ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠብቁ ነው የተናገሩት።

በክረምቱ ወቅት እየተካሄደ ባለው የሰብል ልማት ስራ ከአራት ሚሊዮን በላይ አርሶ አደሮች እየተሳተፉ እንደሚገኙ ከቢሮው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026

ባለፉት አምስት ዓመታት አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ ተችሏል – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ ባለፉት አምስት ዓመታት ስር የሰደዱ ችግሮችን በመቅረፍ አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ መቻሉን የአዲስ...

Jul 18, 2026

በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገበ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገ...

Jun 24, 2026