🔇Unmute
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ) ፦ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት በ5 ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ኮደሮች ኢኒሼቲቭ ዙሪያ ያዘጋጀው የልምድ ልውውጥ መርሐ ግብር ተካሂዷል፡፡
በመርሃ-ግብሩ ላይ የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደሮች ኢኒሼቲቭ ተመራቂ እና የቴክኖሎጂ ሥራ ፈጣሪዋ ማኅሌት ሥዩም በሰጠችው አስተያየት ፕሮግራሚንግን ለማወቅ የግድ የኮምፒውተር ሳይንስ ወይም ልዩ የትምህርት ዘርፍ አያስፈልግም ብላለች።
ሰዎች በእጃቸው ያሉትን የኢንተርኔት እና የቴክኖሎጂ መረጃዎች በመጠቀም እንዲሁም የአካባቢያቸውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች በመተንተን ተግባራዊ መፍትሔ ማምጣት እንደሚችሉ አብራርታለች።
በአሁኑ ወቅት ዲጂታል የትምህርት ቁሳቁሶች እና የመማሪያ አማራጮች በቀላሉ በእጃችን እንደሚገኙ ያነሳችው ማኅሌት፤ ወጣቶች ለዲጂታል ክህሎት ተነሳሽነትንና ጥረትን በማድረግ አበይት ችግሮችን መፍታት እንደሚችሉ ጠቁማለች።
ለዚህም ወጣቶች ዘወትር እውቀታቸውን ማደስ፣ አጫጭር ስልጠናዎችን መውሰድ እንዲሁም ራሳቸውን በዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ማብቃት እንደሚኖርባቸው ገልጻለች።
ለተጨማሪ መረጃ እና ለመመዝገብ፦ ethiocoders.et
#PMOEthiopia #DigitalEthiopia2030 #5MillionEthiopianCoders
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ ባለፉት አምስት ዓመታት ስር የሰደዱ ችግሮችን በመቅረፍ አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ መቻሉን የአዲስ...
Jul 18, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገ...
Jun 24, 2026