🔇Unmute
ጎንደር ፤ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የሚገኙ ከተሞችን ዘላቂ ልማት ለማረጋገጥ የሚያስችል ፕላን ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ፕላን ኢንስቲትዩት አስታወቀ።
ኢንስቲትዩቱ ያለፈው ዓመት አፈጻጸም፣ የ2019 ዕቅድ ትውውቅና የተለያዩ የሕግ ማዕቀፎችን መሠረት ያደረገ የውይይት መድረክ በጎንደር ከተማ እያካሄደ ነው።

በውይይቱ ላይ የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዳይሬክተር ተስፋሁን ተናኜ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ከተሞች ለነዋሪዎቻቸው ምቹ፣ ተወዳዳሪና ዘላቂ ልማት የሚያረጋግጡ እንዲሆኑ እየተደረገ ነው።
ከዚህ ውስጥም የከተሞችን ዕድገት ለማፋጠን በየደረጃው መዋቅራዊ ፕላን በማዘጋጀት እስካሁን ከ137 በላይ ለሚሆኑ ከተሞች የፕላን ዝግጅት ተከናውኗል።
በተጨማሪም፣ ከ31 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የግንባታ ጥያቄዎች በከተሞች ፕላን መሠረት መከናወናቸውን ማረጋገጥ ተችሏል።
ይህም በከተሞች የመንገድ፣ የውኃ፣ የመብራትና ቴሌኮም የመሠረተ ልማት ግንባታዎች እንዲሳለጡ የሚያደርግ መሆኑን አስገንዝበዋል።
በአዲሱ በጀት ዓመትም የተጀመሩ ተግባራትን በማጠናከር፣ የከተሞችን ዕድገትና ዘመናዊነት የሚያረጋግጡ ዕቅዶች ተግባራዊ ይደረጋሉ ነው ያሉት።
በክልሉ ፕላን ኢንስቲትዩት የጎንደር ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ግዛቸው አዳነ በበኩላቸው፣ የከተሞች ፕላን ክለሳ፣ የመዋቅራዊና መሠረታዊ ፕላን ዝግጅት እና የሰፈር ልማት ፕላን ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።
ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ በማዕከላዊ ጎንደር፣ በምዕራብ ጎንደር እና በሰሜን ጎንደር ዞኖች ሥር የሚገኙ ከተሞችን በመከታተል የፕላን ዝግጅትና ትግበራ ድጋፍ እያደረገ ነው ብለዋል።
ከዛሬ ጀምሮ ለሦስት ቀናት በሚካሄደው በዚህ መድረክ ላይ የኢንስቲትዩቱ የሥራ ኃላፊዎችና የቅርንጫፍ አመራሮች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ ባለፉት አምስት ዓመታት ስር የሰደዱ ችግሮችን በመቅረፍ አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ መቻሉን የአዲስ...
Jul 18, 2026