የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ኢትዮጵያ የጨረር ቴክኖሎጂን ከህክምናው በተጨማሪ በተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ላይ እየተጠቀመች ነው

Aug 19, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 12/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የጨረር ቴክኖሎጂን ከህክምናው በተጨማሪ በተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ላይ እየተጠቀመች እንደምትገኝ የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሰሎሞን ጌታቸው (ዶ/ር) ገለጹ።

የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ባለስልጣን በህክምናው ዘርፍ ለምርመራ ዓላማ ጥቅም ላይ እየዋለ በሚገኘው የጨረር ቴክኖሎጂ አገልግሎትን በተመለከተ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ወርክሾፕ አካሂዷል።


በወርክሾፑ ላይ የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሰሎሞን ጌታቸው እንዳሉት ባለስልጣኑ ቁጥጥር ከሚያደርግባቸው ቴክኖሎጂዎች መካከል የጨረር ቴክኖሎጂ አንዱ ነው።

ኢትዮጵያ የጨረር ቴክኖሎጂን በህክምናው ብቻ ሳይሆን በተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ላይ እየተጠቀመች እንደምትገኝም ተናግረዋል።

ዶክተር ሰሎሞን ጌታቸው በጥናታቸው እንዳመላከቱት የጨረር ቴክኖሎጂ ለህክምና ምርመራ ጥቅም ላይ በሚውልበት ወቅት የጨረር መጠን አጠቃቀም ከቦታ ቦታ እና ከባለሙያ ባለሙያ መለያየት መስተዋሉን ጠቁመዋል።

ይህም በጨረራ ቴክኖሎጂ እና በሌሎች የህክምና ባለሙያዎች እንዲሁም የህክምና ተገልጋዮች ላይ የጎንዮሽ ጉዳት ሊያስከትል እንደሚችል ገልጸዋል።

በህክምና ዘርፉ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ትክክለኛውን መጠን ግምት ውስጥ ያስገባ የጨረራ ቴክኖሎጂን ለምርመራም ሆነ ለህክምና አገልግሎትን መጠቀም እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

የጨረር ቴክኖሎጂ ለህክምና ምርመራ ሲውል የታካሚውን ወቅታዊ የጤና እና የአካል ሁኔታ ግምት ውስጥ ማስገባት እንደሚገባ የተናገሩት ደግሞ በጥናቱ በአማካሪነት የተሳተፉት ፕሮፌሰር ሰይፈ ተፈሪ ናቸው።


ጥናቱ ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች እና በህክምናው ዘርፍ መሳተፍ የሚገባቸውን ባለሙያዎች ማሳተፉን ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ በተለያዩ የህክምና ተቋማት የጨረር ቴክኖሎጂን ለህክምና ምርመራ እየተጠቀምን ብንሆንም ወጥ በሆነ መንገድ እየተተገበረ ባለመሆኑ ጥናቱ ይህን ችግር በመፍታት በኩል የራሱን አስተዋጽኦ ያበረክታል ብለዋል።

ሌላኛው በጥናቱ በአማካሪነት የተሳተፉት ፕሮፌሰር ዳንኤል ዘውድነህ በበኩላቸው፤ ጥናቱ በተለያዩ ጊዜያት ሆስፒታሎች በተናጠል ሲያከናውኑት ከነበረው ጥናት በይዘቱም ሆነ በስፋቱ ከፍ ያለ መሆኑን ጠቁመው፤ በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ተናግረዋል።


የጨረር ቴክኖሎጂን ለህክምና ምርመራ ስንጠቀም ለታካሚውም ሆነ ለዘርፉ ባለሙያ ደህንነትን በሚያረጋግጥ መልኩ መሆን እንዳለበትም ጥናቱ ምክረ ሀሳብ ያካተተ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026

ባለፉት አምስት ዓመታት አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ ተችሏል – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ ባለፉት አምስት ዓመታት ስር የሰደዱ ችግሮችን በመቅረፍ አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ መቻሉን የአዲስ...

Jul 18, 2026