🔇Unmute
አዳማ ፤ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ከ18 ሺህ 800 ካሬ ሜትር በላይ የከተማ መሬት ወደ መሬት ባንክ እንዲገባ መደረጉን የክልሉ ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን አስታወቀ።
የክልሉ ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አብደላ ኦገቴ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በተለያዩ ሴክተሮች ሙስና እና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን አንስተዋል።
በክልሉ በመንግስት ተቋማት የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችን አስቀድሞ ለመከላከል የሚያስችሉ 26 የሙስና መከላከል የአሰራር ስርዓት ጥናቶች መካሄዳቸውን ዘርዝረዋል።
የመስኖ ፕሮጀክት ግንባታና የውል አስተዳደር፣ የሕገ-ወጥ ንግድ ክትትል እና የገቢ አሰባሰብ ስርዓት፣ የግል ህክምና ተቋማት የፈቃድ አሰጣጥና ክትትል፣ የአርሶ አደሮች ህብረት ሥራ ማህበራትና ዩኒየኖች የግዥና ሽያጭ አሰራር ጥናቶች የሚገኙበት መሆኑን ጠቅሰዋል።
በተለይም በመሬት ሃብት ላይ የሚደርሰውን ምዝብራ ለመከላከል ብዙ ጥረት መደረጉን አስታውሰው፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 18 ሺህ 849 ካሬ ሜትር የከተማ መሬት ወደ መሬት ባንክ ተመላሽ ተደርጓል ብለዋል።
በዚህም የከተማ መሬትን ከህገ-ወጥ ወረራ፣ ከደላሎች ድብቅ ሽያጭ እና ከአሰራር ብልሹነት በመታደግ ወደ "መሬት ባንክ" ማስገባት፤ መሬቱ ለታለመለት ልማት እንዲውል ማድረግ እየተቻለ ስለመሆኑ አንስተዋል።
በተጨማሪም በየደረጃው ለሚገኙ 6 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዜጎች ግንዛቤ ለማስጨበጥ ታቅዶ፤ ከ10 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑት ተደራሽ በማድረግ ከእቅድ በላይ ማሳካት ስለመቻሉ ተናግረዋል።
የሙስና ወንጀል ህጎች፣ የግዥና ግንባታ አስተዳደር ውል ህጎች፣ የሀብት ማስመለስ አዋጅ፣ የሙያ እና የአመራርነት ሥነ-ምግባር እንዲሁም የመከላከል ስትራቴጂዎች ላይ በማተኮር ግንዛቤ ስለመሰጠቱም አስታውሰዋል።
ከ135 ሺህ በላይ የህዝብ ተመራጮች፣ ተሿሚዎች እና የመንግስት ሰራተኞች በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ የሃብት ምዝገባ ስራ ስለመካሄዱም ገልጸው በተያዘው ዓመትም መሰል ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።
በሀገሪቷ በወጣው የሀብት ማስታወቂያና ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 668/2002 መሠረት ተሿሚዎችና የመንግስት ሰራተኞች ሀብታቸውን እንዲያስመዘግቡ የሚደነግግ መሆኑ ይታወቃል።
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ ባለፉት አምስት ዓመታት ስር የሰደዱ ችግሮችን በመቅረፍ አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ መቻሉን የአዲስ...
Jul 18, 2026