የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ የእንስሳት ዝርያን በማሻሻል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት ውጤት ተመዝግቧል

Aug 26, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አርባምንጭ፤ ነሐሴ 19/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የእንስሳት ዝርያን በማሻሻል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት ውጤት መመዝገቡን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ፡፡

"የእንስሳት ዝርያን ማሻሻል ለላቀ ብልጽግና" በሚል መሪ ሃሳብ በክልሉ የ2019 በጀት ዓመት የእንስሳት ዝርያ ማሻሻያ ስራ ማስጀመሪያ ስነ ስርአት በጋሞ ዞን ዲታ ወረዳ ተካሂዷል።


በስነ ስርአቱ ላይ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ግብርና ቢሮ ሃላፊ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) እንደገለጹት በክልሉ የእንስሳት ዝርያን በማሻሻል ምርታማነትን በማሳደግ በሌማት ትሩፋት መርሀ ግብር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት ውጤት ተመዝግቧል፡፡

በክልሉ የእንስሳት ምርታማነት በመጨመሩም የምግብ ሉዐላዊነትን ለማረጋገጥ አቅም መፍጠሩን አመልክተዋል።

በክልሉ ሰፊ የእንስሳት ሀብት መኖሩን የጠቀሱት መሪሁን ( ዶ/ር ) የእንስሳት ሀብትን በአግባቡ በመንከባከብ ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ለማላቅ የሚከናወኑ ተግራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል፡፡

የእንስሳትን ዝርያ ማሻሻል ስራው በወተት ሀብትና በዝርያ ላይ ከፍተኛ ለውጥ የሚያስገኝ መሆኑን ጠቅሰው የክልሉን አርሶና አርብቶ አደር ተጠቃሚነት ለማሳደግ በሚከናወኑ ተግባራት ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን እንዲወጡ መልዕክት አስተላልፈዋል።


የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምስ አድማሱ (ዶ/ር) የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በዞኑ የምግብ ሉዐላዊነት እንዲረጋግጥ ትልቅ ፋይዳ እያስገኘ ነው ብለዋል።

በዞኑ የወተት ምርታማነት በመጨመሩ ማህበረሰቡ ጥሪት ከማፍራት ባለፈ የአመጋገብ ስርዓቱ ላይ ጉልህ ለውጥ ማሳየቱን ጠቅሰዋል።

እንደ ክልል የተጀመረውን የእንስሳት ዝርያ በማሻሻል ምርታመነትን የማሳደግ መርሃ ግብር በሁሉም ወረዳዎችና ቀበሌዎች ተግባራዊ ለማድረግ በቅንጅት ይሰራል ብለዋል።

በዞኑ በሁሉም አካባቢ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ለማስፋፋት በተከናወኑ ተግባራት 500 የወተት መንደሮች ተፈጥረዋል ያሉት ደግሞ የጋሞ ዞን ግብርና መምሪያ ሃላፊ ማጌሶ ማሾሌ ናቸው።


የእንስሳት ዝርያን በማሻሻል የህዝቡን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማረጋገጥ በትኩረት እንደሚሰራ አመላክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026

ባለፉት አምስት ዓመታት አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ ተችሏል – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ ባለፉት አምስት ዓመታት ስር የሰደዱ ችግሮችን በመቅረፍ አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ መቻሉን የአዲስ...

Jul 18, 2026