የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ የተጀመሩ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች በአዲሱ በጀት አመትም ይበልጥ ተጠናክረው ይቀጥላሉ- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

Aug 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 20/2018 (ኢዜአ)፡-የህዝቡን ጥያቄዎች መሰረት በማድረግ የተጀመሩ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች በአዲሱ በጀት አመትም ይበልጥ ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ።

የአማራ ክልል የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 ዕቅድ የትውውቅ መድረክ በባሕር ዳር ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል።


በመድረኩ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ፈተናዎችን በማለፍና ችግሮችን ወደ እድል በመቀየር ጭምር በሁሉም ሴክተሮች አበረታች የሆኑ ውጤቶች መመዝገባቸውን አንስተዋል።

በተለይም የ25 ዓመት አሻጋሪ የልማት እና የ5 ዓመት ስትራቴጂካዊ ዕቅዶችን ለመተግበር የተደረገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን አንስተው በሁሉም ዘርፍ የሕዝብን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ረገድ ስኬታማ ተግባራት ተከናውነዋል ብለዋል።

የተቋማትን፣ የአመራሩንና የባለሙያውን የመፈጸም አቅም በማሳደግ የተሻለና ተወዳዳሪ ኢኮኖሚ በመገንባት በኩል ተስፋ የሚሰጡ ጅምሮች መኖራቸውንም አንስተዋል።

በመሆኑም የክልሉን ህዝብ ጥያቄ መሰረት በማድረግ የተጀመሩ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች በአዲሱ በጀት አመትም ይበልጥ ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን ተናግረዋል።


በአዲሱ ዓመት አዲስ መንግስት የሚመሰረትበትና ተስፋ የተሰነቀባቸው የልማት ስራዎችም በላቀ ቁርጠኝነት የሚተገበሩበት ይሆናል ብለዋል።

በተጨማሪም በየደረጃው በቴክኖሎጂ የታገዘ ዘመናዊ አሠራርን ተግባራዊ በማድረግ ሕዝብን የሚያረካ አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ ላይ ትኩረት ይደረጋል ብለዋል።

ከቀደሙ ተግዳሮቶች ትምህርት በመውሰድና የተሻሉ ተሞክሮዎችን በማስፋት በአዲሱ በጀት ዓመት የሕዝብን ደኅንነት በአስተማማኝ ሁኔታ የመጠበቅና ዘርፈ-ብዙ ምርታማነትን የማሳደግ ሥራ በትኩረት እንደሚሠራ ገልጸዋል።

የክልሉን ብሎም የሀገርን ኢኮኖሚ በዘላቂነት በሚያሳድጉ ተግባራት ላይ በማተኮር ለስኬታማነቱ የተቀናጀ ጥረት የሚደረግ መሆኑንም ተናግረዋል።

በመሆኑም በየደረጃው ያለው አመራር የጋራ ራዕይ ሰንቆና በተግባራት ዙሪያ ጠንካራ ተግባቦት በመፍጠር በተሻለ ቁርጠኝነት እና በጊዜ የለኝም መንፈስ መስራት እንዳለበት አሳስበዋል።

ለሁለት ቀናት በሚካሄደው የምክክር መድረክ የክልሉ የተለያዩ ተቋማት አመራሮችና ባለሙያዎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026

ባለፉት አምስት ዓመታት አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ ተችሏል – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ ባለፉት አምስት ዓመታት ስር የሰደዱ ችግሮችን በመቅረፍ አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ መቻሉን የአዲስ...

Jul 18, 2026