🔇Unmute
አሶሳ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በመኸር እርሻ እስካሁን 1 ሚሊዮን 632 ሺህ ሄክታር ማሳ በተለያዩ የሰብል አይነቶች መልማቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
በተለይም እስካሁን ከለማው መሬት 231 ሺህ 902 ሄክታሩ በቅባት እህሎች የተሸፈነ መሆኑ ተመላክቷል።
በክልሉ ግብርና ቢሮ የሰብል ልማትና ጥበቃ ቴክኖሎጂ ማስፋፊያ ዳይሬክተር ፍቅሩ አቡን ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ በመኸር ወቅቱ 1 ነጥብ 8 ሚሊየን ሄክታር መሬት በተለያዩ የሰብል አይነቶች ለማልማት ታቅዶ ተግባራዊ እየተደረገ ነው።
እስካአሁን በተካሄደ የእርሻ ስራ 1 ሚሊየን 632 ሺህ ሄክታር ማሳ በተለያዩ የሰብል አይነቶች መልማቱን ተናግረዋል።
ከለማው ማሳ ውስጥም 231 ሺህ 902 ሄክታሩ በሰሊጥ፣ አኩሪ አተር እንዲሁም ለውዝ በመሳሰሉ የቅባት እህሎች የተሸፈነ መሆኑን ለአብነት ጠቅሰዋል።
አርሶ አደሮች በክልሉ ከሚገኘው የዘይት ፋብሪካ ጋር የገበያ ትስስር በመፈጠሩ የቅባት እህሎችን በስፋት በማምረት ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በክልሉ የቅባት እህሎችን ምርታማነትን ለማሳደግ የተሻሻሉ ዝርያዎችን በመጠቀም እንዲሁም ለአርሶ አደሩ ተገቢውን ግንዛቤ በመፍጠር ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ ነው ብለዋል።
በክልሉ ለቅባት እህሎች ተስማሚ የሚሆነውን የአካባቢ ስነምህዳር የመለየት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከአርሶ አደሩ በተጨማሪ በእርሻ ኢንቨስትመንት የተሰማሩ ባለሃብቶች በሰፋፊ የእርሻ ማሳ ላይ የቅባት እህሎችን በማምረት ለገበያ እያቀረቡ መሆናቸውን አስታውቀዋል።
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ ባለፉት አምስት ዓመታት ስር የሰደዱ ችግሮችን በመቅረፍ አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ መቻሉን የአዲስ...
Jul 18, 2026