የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>ኢትዮጵያ የዓለም ስልጣኔ ፈር ቀዳጅ እና በፈጣን የኢኮኖሚ እድገት ላይ በመገኘቷ ለጥምረቱ የአፍሪካ ቢሮ መቀመጫነት ተመርጣለች - ፕሮፌሰር ጄፍሪ ሳክስ</p>

Feb 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤የካቲት 10/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የዓለም ስልጣኔ ፈር ቀዳጅ እና በፈጣን የኢኮኖሚ እድገት ላይ መገኘቷ የተመድ የዘላቂ ልማት መፍትሔ ጥምረት ለአፍሪካ ቢሮ መቀመጫነት መመረጧን የጥምረቱ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ጀፍሪ ሳክስ ገለጹ፡፡


የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት(ተመድ) የዘላቂ ልማት መፍትሔ ጥምረት የአፍሪካ ቢሮውን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መክፈቱን ዛሬ ይፋ አድርጓል፡፡


የተመድ የዘላቂ ልማት መፍትሔ ጥምረት ለዘላቂነት ልማት እንቅፋት የሆኑ ጉዳዮችን ለመፍታት በዓለም ዙሪያ ያሉ የፈጠራ ልሂቃንና የቴክኒክ ባለሙያዎች የሚያሰባስብ ነው፡፡


በአዲስ አበባ የተከፈተው የጥምረቱ ቢሮም የጥናትና ምርምር ሥራዎችን በማከናወን ለፖሊሲ አውጭዎች ግብዓት የሚሆኑ ሳይንሳዊ መፍትሔዎችን ያቀርባል ተብሏል።


አሜሪካዊው የምጣኔ ሀብት ባለሙያ እና የተመድ የዘላቂ ልማት መፍትሔ ጥምረት ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ጀፍሪ ሳክስ እንዳሉት፣ የጥምረቱ ተቀዳሚ ዓላማ በዓለም ላይ ኢኮኖሚያዊ ብልጽግና እና ማህበራዊ ፍትህ ማስፈን ነው።


ጥምረቱ በአሜሪካ ኒውዮርክ፤ በአውሮፓ ፓሪስ እና በኤዥያ ኳራላምፑር ቀጣናዊ ማስተባበሪያዎች እንዳሉት ገልጸው፥ አራተኛው የአፍሪካ ማስተባበሪያ ቢሮ በአዲስ አበባ ዛሬ በይፋ መከፈቱን ተናግረዋል፡፡


ኢኮኖሚያዊ እድገት፣ማሕበራዊ ፍትህ፣የአየር ንብረት ጥበቃ እና የዘላቂ የልማት ግቦች አላማዎች መሆናቸውን ገልጸዋል።


የዘላቂ ልማት መፍትሔ ጥምረት ግቡ የዘላቂ የልማት ግቦችን ማሳካት መሆኑን ገልጸው፥ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በምርምሮቻቸው፣ በአግልግሎታቸው መንግስታትን የሚደግፉ መፍትሔዎች ላይ ማተኮር አለባቸው ብለዋል፡፡


አፍሪካ በቀጣዮቹ 40 ዓመታት ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት በማስመዝገብ የዓለም ኢኮኖሚ ማዕከል ትሆናለች ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ ጥምረቱ የአፍሪካን ዘላቂ ልማትና ሰላም አጠናክሮ ማስቀጠል የሚያስችል ፕሮጀክት መሆኑንም ገልጸዋል፡፡


ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት መስራችና አባል፣ የተለያዩ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ተቋማት መገኛ እንዲሁም የቀደምት ሥልጣኔ ፈር ቀዳጅ መሆኗን ተናግረዋል።


በመሆኑም ኢትዮጵያ የዓለም ስልጣኔ ፈር ቀዳጅ እና በፈጣን የኢኮኖሚ እድገት ላይ መገኘቷ የተመድ የዘላቂ ልማት መፍትሔ ጥምረት ለአፍሪካ ቢሮ መቀመጫነት መርጠናታል ብለዋል፡፡


ፕሮፌሰር ጀፍሪ ሳክስ እንደ አንድ የምጣኔ ሀብት ባለሙያ በኢትዮጵያ እየተመዘገበ እንዳለው ፈጣን ኢኮኖሚያዊ እድገት የሚያስደስት ነገር የለም ብለዋል።


የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ(ዶ/ር) የዘላቂ የልማት ግቦች የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063ን ከግብ ለማድረስ ቁልፍ መሳሪያ መሆኑን ተናግረዋል።


ዩኒቨርሲቲው በጥናትና ምርምር የላቀ አገልግሎት እንዳለው ገልጸው፤ የዘላቂ ልማት መፍትሔ ጥምረት ግቦችን ለማሳካት ተጨማሪ አቅም ይፈጥራል ብለዋል።


የመፍትሔ ጥምረቱ ቢሮ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መከፈቱ ትልቅ ትርጉም እንዳለው ገልጸው፤ የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ የዩኒቨርሲቲውን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ የጎላ አበርክቶ እንዳለውም አንስተዋል።


ዩኒቨርሲቲው በስትራቴጂክ እቅዱ ዓለም አቀፍ ትብብሮቹ ችግር ፈቺ እና ተጽዕኖ ፈጣሪ እንዲሆኑ ማስቻል ነው ብለዋል።


ኢትዮጵያ ከዘላቂ የልማት መፍትሔ ጥምረት ማግኘት የሚገባትን ጥቅም እንድታገኝ የሚያስችል ጥረት እንደሚያደርጉም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026