የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በገንዳውሃ ከተማ አስተዳደር ከ60 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የጎርፍ መከላከያ ግንባታዎች እየተከናወኑ ነው

May 12, 2025

IDOPRESS

ገንዳ ውሃ፤ ግንቦት 3/2017(ኢዜአ)፡-በገንዳ ውሃ ከተማ አስተዳደር ከ60 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የጎርፍ መከላከያ ግንባታዎች እየተከናወኑ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ የቤቶች፣ ኮንስትራክሽንና መሰረተ ልማት ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

በጽህፈት ቤቱ የመሰረተ ልማት ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ታረቀኝ አለማየሁ ለኢዜአ እንደገለጹት በከተማው በጎርፍ አደጋ ተደጋጋሚ ጉዳት የሚደርስባቸውን አካባቢዎች በመለየት የጎርፍ ቅድመ መከላከል ሥራዎች እየተከናወኑ ነው።


በከተማዋ መካከል አቋርጦ የሚያልፈው የገንዳ ውሃ ወንዝ በክረምት ወቅት ሞልቶ ሲፈስ በከተማዋ በንብረትና በማሳ ላይ በተዘራ ሰብል ላይ ጉዳት ሲያደስር እንደነበረ አስታውሰዋል።

በመጪው ክረምት መሰል ችግር እንዳይከሰት ለመከላከል ከ60 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተለያዩ የጎርፍ መከላከያ ግንባታ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም የአራት ኪሎ ሜትር የአዲስ መንገድ ከፈታ፣ የጎርፍ መፋሰሻና መቀልበሻ ትቦ ግንባታ ሥራዎች እንዲሁም የሁለት አነስተኛ ድልድዮችና መሰል ሥራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን አስረድተዋል።

ከገንዳ ውሃ ከተማ ነዋሪዎች መካከል የቀበሌ 1 ነዋሪ አቶ ወንድማገኝ በየነ ባለፈው የክረምት ወቅት በደረሰ የጎርፍ አደጋ በቤታቸው ውስጥ የነበረ 10 ኩንታል አኩሪ አተር መበላሸቱን አስታውሰዋል።

የከተማ አስተዳደሩ ይሄን ችግር ተገንዝቦ ዘንድሮ የጎርፍ መውረጃ ትቦ መስራቱ ለቀጣይ ክረምት ከአደጋ ስጋት እንደታደጋቸው ተናግረዋል።


በከተማው ቀበሌ 2 የሚኖሩት ወይዘሮ ጥሩዬ አበባው በበኩላቸው እየተሰራ ያለው የጎርፍ መከላከያና መፋሰሻ ትቦ ከጎርፍ ስለሚታደጋቸው ከስጋት ነጻ መሆናቸውን ገልፀዋል።

በየዓመቱ ክረምት በመጣ ቁጥር ጭንቀት ውስጥ ይገቡ እንደነበር አስታውሰው፣ መንግስት ችግሩን ለመፍታት ባከናወናቸው የጎርፍ መከላከያ ስራዎች ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።

"ከተማ አስተዳደሩ በዚህ ዓመት አዲስ መንገድ በመክፈት በክረምት ከሚገጥም የመንገድ ችግርና የጎርፍ አደጋ ስጋት ታድጎናል" ያሉት ደግሞ የቀበሌ 01 ነዋሪ ወይዘሮ አልማዝ ገብሬ ናቸው፡፡

በአካባቢያቸው በየዓመቱ በሚከሰት የጎርፍ አደጋ በንብረት ላይ አንዳንዴም በሰው ህይወት ላይ ጉዳት ይከሰት እንደነበር አስታውሰው፣ ዘንድሮ በአካባቢያቸው የተሰራ የጎርፍ መከላከያ ከስጋት እንደታደጋቸው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026