
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦ በዘንድሮው ዓመት 900 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 42ኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እያካሄደ ይገኛል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በስብሰባው የመንግስትን የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃጸም አስመልክቶ ከምክር ቤቱ አባላት ለሚነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ ገቢን በተመለከተ በዘንድሮ አመት 900 ቢሊየን ብር ገቢ ማስገባት መቻሉን ተናግረዋል።
1 ነጥብ 2 ትሪሊየን ወጪ መውጣቱን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታውቀው፣ በገቢና ወጭ መካከል የ300 ቢሊየን ብር ልዩነት እንዳለ ተናግረዋል።
ገቢ ግብር ብቻ ሳይሆን ልዩ ልዩ ገቢ እንዳለ የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ነገር ግን ከገቢ ግብር የተገኘው አጠቃላይ ሃብት ከወጪ አንፃር ዝቅተኛ ነው ብለዋል።
ይህ ሊሆን የቻለው ታክስ ከጥቅል ሀገራዊ ምርት ያለው ጥምርታ በአፍሪካ ስታይ 14 በመቶ መሆኑን ገልፀዋል።
ከትርፍና ከካፒታል ገቢ አንፃር ሲታይ አፍረካ ላይ 6 ነጥብ 2 በመቶ ነው ብለዋል።
የኪሳራ ሪፖርት በማቅረብ፣ ትርፍ አላገኘሁም በማለትና ሪፖርት ባለማቅረብ ምክንያት 46 ሺህ የሚጠጉ የታክስ ተመዝጋቢዎች ኢትዮጵያ ውስጥ ግብር እንደማይከፍሉ አስታውቀዋል።
ኢትዮጵያ ውስጥ ንግድ ፈቃድ ወስደው ግብር መክፈል ከሚገባቸው እየከፈሉ ያሉት 37 በመቶ ብቻ ናቸው ብለዋል።
እነዚህም እየከፈሉ ያሉት 60 በመቶውን ብቻ እንደሆነና ቀሪውን 40 በመቶ እየከፈሉ ያሉት የመንግስት ልማት ድርጅቶች እንደሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።
ከታክስ አስተዳደር ጋር ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ ሪፎርም እየተሰራ እና ለውጥ እየታየበት እንዳለ ተናግረው ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
እንዲሁም የግብር ስወራ እና ህገ ወጥ ግብይት ላይ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የሪፎርም ስራ እየተሰራ እና ለውጥ እየታየበት መሆኑን ጠቁመው ምክር ቤቱ ድጋፉን እንዲያጠናክር ጠይቀዋል።
እንዲሁም በንግድ ስራ ላይ የተሰማሩ ዜጎች ግብር በታማኝነት እንዲከፍሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥሪ አቅርበዋል።
አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...
Sep 14, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026