የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በከተማው ተገንብተው ለአገልግሎት የበቁት የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ለጥያቄያችን ምላሽ የሰጡ ናቸው - የመቱ ከተማ ነዋሪዎች

Jul 4, 2025

IDOPRESS

መቱ፤ ሰኔ 26/2017 (ኢዜአ)፡-በመቱ ከተማ ተገንብተው ለአገልግሎት የበቁት የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ለረጅም ጊዜ ጥያቄያቸው ምላሽ የሰጡ መሆናቸውን ነዋሪዎች ገለጹ።

በመቱ ከተማ ከ329 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ በጀት የተገነቡ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች የኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል።


በምረቃው ወቅት ኢዜአ ያነጋገራቸው የከተማው ነዋሪዎች ፤ ለአገልግሎት የበቁት የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች የረጅም ጊዜ ጥያቄያቸውን የመለሱ እና ተጠቃሚነታቸውንም የሚያሳድጉ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ከነዋሪዎቹ መካከል አቶ ታከለ ዳዲ ፤ የተገነቡት ፕሮጀክቶች ለመሰረተ ልማት ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡ ናቸው ብለዋል።

በተለይም የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች ግንባታ ትውልዱ ከመጀመሪያ አንስቶ የተሻለ እውቀት መጨበጥ እንዲችል እድል የሚፈጥሩ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

በከተማው ለአገልግሎት የበቁ የገበያ ማዕከላት ፣ የመስሪያ እና መሸጫ ሼዶች ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴን የሚያሳድጉ በመሆናቸው ጠቀሜታቸው የጎላ ነው ብለዋል።



ሌላኛው የከተማው ነዋሪ አቶ ኦልጂራ ሂርኪሳ በበኩላቸው፤ በቀደሙት ዓመታት በከተማው የሚጀመሩ የመሰረተ ልማት ተቋማት ግንባታዎች የሚጓተቱና ተጀምረውም የሚቆሙ እንደነበሩ አስታውሰዋል።

ባለፉት ጥቂት ዓመታት ግን የከተማውን ነዋሪ ተጠቃሚ የሚያደርጉ ትምህርት ቤት፣ የአገልግሎት መስጫ ማዕከላትና የመስሪያ ሼዶች በአጭር ጊዜ እየተገነቡ ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች የነዋሪውን ተጠቃሚነት ከማሳደግ ባለፈ ለከተማዋ እድገትም ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክቱ ጠቅሰው ፤ ለረጅም ጊዜ አገልግሎት እንዲሰጡ መጠበቅ እና መንከባከብ ከሁላችንም ይጠበቃል ብለዋል።

በፕሮጀክቶች ምረቃ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነመራ ቡሊ፣ በክልሉ የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያግዙ የግንባታ ተግባራት የተለየ ትኩረት ተሰጥቷቸው እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልጸዋል።


በተለይም በከተሞች እየተከናወኑ የሚገኙ የመሠረተ ልማት አውታሮች ለነዋሪው የስራ ዕድል መፍጠር ጭምር የሚያስችሉ መሰረተ ልማቶች በስፋት ተጠናክረው መቀጠላቸውን ተናግረዋል።

የመቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ተሻለ ኤጄርሶ፤ በከተማው ከ329 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ በጀት የተገነቡ 44 የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት ክፍት መደረጋቸውን ተናግረዋል።


ፕሮጀክቶቹ የከተማ ውበትን እየጠበቁ የስራ ዕድልን መፍጠር የሚያስችሉ እንዲሁም የነዋሪዎቹን ማሕበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ መሆናቸውንም ገልጸዋል።


ዛሬ የተመረቁትም የ'ቡኡራ ቦሩ' የተሰኙ ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች፣ የከተማ ግብርና ክላስተሮች፣ የገበያ ማዕከል ሼዶችን ጨምሮ ሌሎችም የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች መሆናቸውን አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026