
ሐረር፤ ሐምሌ 2/2017(ኢዜአ)፦ የሐረር ከተማ የኮሪደር ልማት ስራዎች ቃል በተግባር የተገለጸባቸው ናቸው ሲሉ በብልፅግና ፓርቲ የዋናው ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ መለስ አለሙ ገለጹ።
አቶ መለስ አለሙን ጨምሮ የፓርቲው የወጣቶችና ሴቶች ክንፍ እና ሌሎች አመራሮች በሐረር ከተማ የተከናወኑ የኮሪደርና ሌሎች የልማት ስራዎችት ተመልክተዋል።
በወቅቱም አቶ መለስ አለሙ እንደገለጹት በከተማው የተከናወኑ የኮሪደር ልማት ስራዎች ቃል በተግባር የተገለጸባቸው ናቸው።

በአንድ ዓመት ውስጥ የተከናወኑ የኮሪደር እና ሌሎች የልማት ስራዎች ለሰው ልጅ ምቹ ሆነው የተሰሩና ሀገሪቱም ትልቅ ተስፋ ሰንቃ እየሰራች መሆኑን የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል።
አመራሩና ህዝቡ ከተሞቻቸውን ለማልማት በቁርጠኝነት እየሰሩና አዲስ ምዕራፍ መክፈታቸውን በግልጽ የሚያመላክት ነው ሲሉም ተናግረዋል።
ይህም አመራሩና ህብረተሰቡ በልማቱ ላይ ሚናቸው እጅግ ከፍተኛ እንደነበር የሚያሳይ መሆኑን ተናግረው ተጠናክሮ መቀጠል ይገባዋል ብለዋል።
በአመራሩ ታታሪነትና በህብረተሰቡ ተባባሪነት በከተማው የተገነቡት የኮሪደር ልማት ስራዎች የከተማውን ገጽታ የቀየሩና ውብና ጽዱ ሆኖ እንዳገኙት የተናገሩት ደግሞ በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ሴቶች ክንፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ እሌኒ አባይ ናቸው።

የብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ምክትል ፕሬዝዳንትና የጽህፈት ቤት ሃላፊ ወጣት ኡባንግ ኩመዳን በበኩላቸው በከተማው የተከናወነው የኮሪደር ልማት ቅርሶች ተጠብቀው ለትውልድ እንዲተላለፉ ባስቻለ መልኩ መሆኑን ተናግረዋል።
በብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮዽያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ወጣቶች ክንፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ወጣት አብዱል ድንቁ በበኩሉ በከተማው የተከናወኑት የኮሪደር ልማት ስራዎች ውብ ማራኪና የብልጽግና ጉዞን የሚያረጋግጡ ናቸው ብሏል።
አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...
Sep 14, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026