የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የሐረር ከተማ የኮሪደር ልማት ስራዎች ቃል በተግባር የተገለጸባቸው ናቸው

Jul 10, 2025

IDOPRESS

ሐረር፤ ሐምሌ 2/2017(ኢዜአ)፦ የሐረር ከተማ የኮሪደር ልማት ስራዎች ቃል በተግባር የተገለጸባቸው ናቸው ሲሉ በብልፅግና ፓርቲ የዋናው ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ መለስ አለሙ ገለጹ።

አቶ መለስ አለሙን ጨምሮ የፓርቲው የወጣቶችና ሴቶች ክንፍ እና ሌሎች አመራሮች በሐረር ከተማ የተከናወኑ የኮሪደርና ሌሎች የልማት ስራዎችት ተመልክተዋል።

በወቅቱም አቶ መለስ አለሙ እንደገለጹት በከተማው የተከናወኑ የኮሪደር ልማት ስራዎች ቃል በተግባር የተገለጸባቸው ናቸው።


በአንድ ዓመት ውስጥ የተከናወኑ የኮሪደር እና ሌሎች የልማት ስራዎች ለሰው ልጅ ምቹ ሆነው የተሰሩና ሀገሪቱም ትልቅ ተስፋ ሰንቃ እየሰራች መሆኑን የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል።

አመራሩና ህዝቡ ከተሞቻቸውን ለማልማት በቁርጠኝነት እየሰሩና አዲስ ምዕራፍ መክፈታቸውን በግልጽ የሚያመላክት ነው ሲሉም ተናግረዋል።

ይህም አመራሩና ህብረተሰቡ በልማቱ ላይ ሚናቸው እጅግ ከፍተኛ እንደነበር የሚያሳይ መሆኑን ተናግረው ተጠናክሮ መቀጠል ይገባዋል ብለዋል።

በአመራሩ ታታሪነትና በህብረተሰቡ ተባባሪነት በከተማው የተገነቡት የኮሪደር ልማት ስራዎች የከተማውን ገጽታ የቀየሩና ውብና ጽዱ ሆኖ እንዳገኙት የተናገሩት ደግሞ በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ሴቶች ክንፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ እሌኒ አባይ ናቸው።


የብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ምክትል ፕሬዝዳንትና የጽህፈት ቤት ሃላፊ ወጣት ኡባንግ ኩመዳን በበኩላቸው በከተማው የተከናወነው የኮሪደር ልማት ቅርሶች ተጠብቀው ለትውልድ እንዲተላለፉ ባስቻለ መልኩ መሆኑን ተናግረዋል።

በብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮዽያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ወጣቶች ክንፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ወጣት አብዱል ድንቁ በበኩሉ በከተማው የተከናወኑት የኮሪደር ልማት ስራዎች ውብ ማራኪና የብልጽግና ጉዞን የሚያረጋግጡ ናቸው ብሏል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026