የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በበጀት ዓመቱ ከ600 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለዓለም ገበያ ለማቅረብ ታቅዶ እየተሰራ ነው

Jul 17, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ ፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ):- በአዲሱ በጀት ዓመት ከ600 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለዓለም ገበያ በማቅረብ ከ3 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ለማግኘት ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታወቀ።

የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ወደ ውጭ ከተላከ ቡና ከ2 ነጥብ 65 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል፡፡

በተጀመረው አዲስ በጀት ዓመት ከ600 ሺህ ቶን በላይ ቡና ወደ ውጭ በመላክ ከ3 ቢሊዮን ዶላር በላይ ለማግኘት ታቅዶ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡


ወደ ውጭ ለመላክ የታቀደው የቡና መጠን ከተጠናቀቀው የ2017 በጀት ዓመት የ150 ሺህ ቶን ጭማሪ እንዳለው የገለጹት ዳይሬክተሩ፣ ወደውጭ የሚላከው የቡና መጠን በየዓመቱ እያደገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ዘርፉ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ለማሳደግ አርሶ አደሩ ማሳውን እንዲያድስ፣ ያረጁ የቡና ተክሎችን እንዲጎነድል እንዲሁም ልማቱን በጥራትና በስፋት እንዲያከናውን እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

እንደሀገር የቡና ምርትና ምርታማነት የማሳደግ፣ ጥራትን የማስጠበቅና ግብይትን የማዘመን ሥራዎች ላይ በማተኮር በዘርፉ እየተመዘገቡ ያለውን ውጤቶችን የሚያስቀጥሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑንም ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡

የቡና ጥራትን ለማስጠበቅ አዲስ የኤክስቴንሽን ፓኬጅ ተቀርጾ ወደ ስራ መግባቱን የገለጹት ዳይሬክተሩ፣ ባለስልጣኑ ከክልሎች ጋር በመቀናጀት የአርሶ አደሩን ግንዛቤ የሚያሳድጉ ስልጠናዎችን እየሰጠ መሆኑንም ተናግረዋል።

የሲዳማ ክልል ቡና ፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መስፍን ቃሬ በበኩላቸው ከክልሉ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ38 ሺህ 500 ቶን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡን ተናግረዋል፡፡


ከቀረበው ቡናም ከ90 ከመቶ በላይ የሚሆነው ደረጃ 1 እና 2 መሆኑን ጠቁመው በ2018 በጀት ዓመት ከ40 ሺህ 169 ቶን በላይ ቡና ለማቅረብ ታቅዶ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

ለዚህም የቡና ምርትና ምርታማነት የሚጨምሩ ፓኬጆችን የመተግበር፣ የተፈጥሮ ማዳበሪያ በተደራጀ መንገድ የማዘጋጀትና በጥምር ደን የማምረት ሥራው እንደሚጠናከር ገልጸዋል፡፡

በክልሉ የቡና ቴክኖሎጂ መንደሮችን በክላስተር በማደራጀት 18 ሺህ ሄክታር መሬት መልማቱን ጠቁመው በአዲሱ በጀት ዓመትም ይህንን ተግባር የማስፋት ሥራ ይሰራል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026