የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በክልሉ ከቱሪዝም ዘርፍ ከ1 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል

Jul 25, 2025

IDOPRESS

ወልቂጤ፤ሐምሌ 17/2017(ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከቱሪዝም ዘርፍ ከ1 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለፁ።

ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ ምክር ቤት የክልሉን መንግስት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ሲያቀርቡ እንዳመለከቱት፥ የክልሉን የገቢ አቅም የማሳደግና ያሉትን አማራጮች አሟጦ ለመጠቀም የተደረጉ ጥረቶች ውጤታማ ናቸው።


በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የክልሉን ኢኮኖሚ ለማሳደግ ያሉ አቅሞችን ለይቶ ወደስራ በመገባቱና ትኩረት ተሰጥቶ በመሰራቱ ውጤት መገኘቱን ተናግረዋል።

በተለይም በቱሪዝም ዘርፍ በክልሉ ያሉ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ የቱሪስት መስህቦችን በማልማትና በማስተዋወቅ ገቢን ለማጠናከር ግብ ተይዞ ወደ ሥራ መገባቱን አስታውሰዋል።

በዚህም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 13 ሺህ 698 የውጭ ሃገር ቱሪስቶች እና 755 ሺህ 689 የሀገር ውስጥ ቱሪስቶች ክልሉን እንደጎበኙ የተናገሩት እንዳሻው (ዶ/ር)፣በዚህም ከ1 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል ብለዋል።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከተለያዩ የገቢ አርዕስቶች 16 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ገቢ ቢሰበሰብም የክልሉ ኢኮኖሚ ከሚያመነጨው አንጻር የበለጠ ገቢ መሰብሰብ የሚያስችል ዕድል አለ።

ያለ ደረሰኝ የሚደረግ ግብይት፣ የግብር ስወራና ለዚህ ተባባሪ የሚሆኑ የዘርፉ አካላት ችግር እየፈጠሩ መሆኑን ገልጸው፣ ችግሩን ለመፍታት የግንዛቤና የህግ ማስከበር ሥራ መሰራቱን ተናግረዋል።

በተደረገ ፍተሻ ያለደረሰኝ ግብይት ሲፈጽሙና በሌሎች ተገቢ ባልሆነ ተግባር ላይ ተሰማርተው በተገኙ 784 ግብር ከፋዮች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዷል ብለዋል።

በዚህም ተሰውሮ የነበረ 99 ሚሊዮን የታክስ ግኝትን ለማስመለስ ተችሏል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ለችግሩ ምክንያት ናቸው በተባሉ 164 ፈጻሚዎች ላይም አስተዳደራዊና ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን ጠቁመዋል።

በክልሉ 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ''በአንድ ከተማ አንድ ፕሮጀክት ኢኒሼቲቭ" በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑንም አስታውሰዋል።

የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄን መነሻ በማድረግ በክልሉ አስር መዋቅሮች ሞዴል የህዝብ መጸዳጃ ቤቶች ግንባታ ወደ ተግባር መገባቱንም ርዕሰ መስተዳድሩ በሪፖርታቸው አመላክተዋል።

ለዚህም ከህብረተሰቡ ከ623 ሚሊዮን 274 ሺህ በላይ ሀብት ለማሰባሰብ መቻሉን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026