
ሮቤ ፤ሐምሌ 22/2017 (ኢዜአ)፦በባሌ ዞን ከግብርና ወደ ኢንቨስትመንት ለተሸጋገሩ 98 አርሶ አደሮች እና ማህበራት የኢንቨስትመንት ፍቃድ ዛሬ መስጠቱን የዞኑ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ጽህፈት ቤት ገለጸ።
የዞኑ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መሐመድ ኢብሮ እንዳሉት በዞኑ ከግብርና ወደ ኢንቨስትመንት በመሸጋገር እውቅና ያገኙት 98 አርሶ አደሮች፣ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችና ማህበራት ናቸው።

አርሶ አደሮቹና ኢንተርፕራይዞቹ ባለፉት ዓመታት በተሰማሩበት የሥራ መስክ ውጤታማ ከመሆን ባሻገር ከ110 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል ማስመዝገባቸውን ተናግረዋል።
ፕሮጀክቶቹ ወደ ሥራ ሲገቡ 3 ሺህ ለሚጠጉ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ እድል እንደሚፈጥሩም አክለዋል።
በዞኑ አርሶ አደሩ በመደበኛነት ከሚያመርተው ሰብል በተጓዳኝ የተለያዩ ኢኒሼቲቮችን ተግባራዊ በማድረግ ከግብርና ወደ ኢንቨስትመንት የሚሸጋገሩ አርሶ አደሮች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን የገለጹት ደግሞ በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ተወካይ አቶ ሙክታር ማሚያ ናቸው።
ከግብርና ወደ ኢንቨስትመንት የተሸጋገሩ አርሶ አደሮችና ማህበራት በሚሰማሩበት የስራ መስክ ውጤታማ እንዲሆኑ የመሬት አቅርቦትና ሌሎች የተለያዩ ማበረታቻዎች እንደሚደረግላቸውም አመልክተዋል።
ባለፉት ዓመታት በተሰማሩበት የሥራ መስክ ውጤታማ በመሆን ወደ ኢንቨስትመንት ከተሸጋገሩ አርሶ አደሮች መካከል አቶ ሬድዋን ሀጂ ማህሙድ፤ በግብርና ላይ በመሰማራት በሚያመርቱት ሰሊጥና ለውዝ ውጤታማ በመሆን እውቅና ማግኘታቸውን ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅት ወደ ኢንቨስትመንት በመሸጋገራቸው 10 ሄክታር መሬት በኢንቨስትመንት ማበረታቻነት ማግኘታቸውን ገልፀዋል።

በአካባቢው ከሚመረተው የስንዴ ምርት በተጨማሪ ገበያን ማዕከል በማድረግ የተለያዩ የገቢ ማስገኛ ኢኒሼቲቮችን ተግባራዊ በማድረግ ወደ ኢንቨስትመንት መሸጋገራቸውን የገለጹት ደግሞ ሌላው አርሶ አደር በሺር ሐጂ ኢስማኤል ናቸው።
በአሁኑ ወቅት በኢንቨስትመንት ማበረታቻነት የተሰጣቸው 10 ሄክታር መሬትና የእውቅና ሰርተፊኬት ይበልጥ ለተሻለ ሥራ እንዳነሳሳቸውም አክለዋል።
በባሌ ዞን ሽግግር ያደረጉትን ጨምሮ ከ2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 364 ባለሃብቶች በተለያዩ የኢንቨስትመንት አማራጮች መሰማራታቸውን ከዞኑ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ጽህፈት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026