የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በዞኑ ከግብርና ወደ ኢንቨስትመንት ለተሸጋገሩ 98 አርሶ አደሮች እና ማህበራት የኢንቨስትመንት ፍቃድ ተሰጠ

Jul 30, 2025

IDOPRESS

ሮቤ ፤ሐምሌ 22/2017 (ኢዜአ)፦በባሌ ዞን ከግብርና ወደ ኢንቨስትመንት ለተሸጋገሩ 98 አርሶ አደሮች እና ማህበራት የኢንቨስትመንት ፍቃድ ዛሬ መስጠቱን የዞኑ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ጽህፈት ቤት ገለጸ።

የዞኑ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መሐመድ ኢብሮ እንዳሉት በዞኑ ከግብርና ወደ ኢንቨስትመንት በመሸጋገር እውቅና ያገኙት 98 አርሶ አደሮች፣ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችና ማህበራት ናቸው።


አርሶ አደሮቹና ኢንተርፕራይዞቹ ባለፉት ዓመታት በተሰማሩበት የሥራ መስክ ውጤታማ ከመሆን ባሻገር ከ110 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል ማስመዝገባቸውን ተናግረዋል።

ፕሮጀክቶቹ ወደ ሥራ ሲገቡ 3 ሺህ ለሚጠጉ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ እድል እንደሚፈጥሩም አክለዋል።

በዞኑ አርሶ አደሩ በመደበኛነት ከሚያመርተው ሰብል በተጓዳኝ የተለያዩ ኢኒሼቲቮችን ተግባራዊ በማድረግ ከግብርና ወደ ኢንቨስትመንት የሚሸጋገሩ አርሶ አደሮች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን የገለጹት ደግሞ በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ተወካይ አቶ ሙክታር ማሚያ ናቸው።

ከግብርና ወደ ኢንቨስትመንት የተሸጋገሩ አርሶ አደሮችና ማህበራት በሚሰማሩበት የስራ መስክ ውጤታማ እንዲሆኑ የመሬት አቅርቦትና ሌሎች የተለያዩ ማበረታቻዎች እንደሚደረግላቸውም አመልክተዋል።

ባለፉት ዓመታት በተሰማሩበት የሥራ መስክ ውጤታማ በመሆን ወደ ኢንቨስትመንት ከተሸጋገሩ አርሶ አደሮች መካከል አቶ ሬድዋን ሀጂ ማህሙድ፤ በግብርና ላይ በመሰማራት በሚያመርቱት ሰሊጥና ለውዝ ውጤታማ በመሆን እውቅና ማግኘታቸውን ተናግረዋል።

በአሁኑ ወቅት ወደ ኢንቨስትመንት በመሸጋገራቸው 10 ሄክታር መሬት በኢንቨስትመንት ማበረታቻነት ማግኘታቸውን ገልፀዋል።


በአካባቢው ከሚመረተው የስንዴ ምርት በተጨማሪ ገበያን ማዕከል በማድረግ የተለያዩ የገቢ ማስገኛ ኢኒሼቲቮችን ተግባራዊ በማድረግ ወደ ኢንቨስትመንት መሸጋገራቸውን የገለጹት ደግሞ ሌላው አርሶ አደር በሺር ሐጂ ኢስማኤል ናቸው።

በአሁኑ ወቅት በኢንቨስትመንት ማበረታቻነት የተሰጣቸው 10 ሄክታር መሬትና የእውቅና ሰርተፊኬት ይበልጥ ለተሻለ ሥራ እንዳነሳሳቸውም አክለዋል።

በባሌ ዞን ሽግግር ያደረጉትን ጨምሮ ከ2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 364 ባለሃብቶች በተለያዩ የኢንቨስትመንት አማራጮች መሰማራታቸውን ከዞኑ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ጽህፈት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026