የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በቻይና እና አፍሪካ መካከል የሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ትብብር እየተጠናከረ መጥቷል

Nov 7, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 27/2018(ኢዜአ)፦ በቻይና እና አፍሪካ መካከል የሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ትብብር እየተጠናከረ መምጣቱን በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የግብርና፣ ገጠር ልማት ብሉ ኢኮኖሚና ዘላቂ ልማት ዲፓርትመንት ፖሊሲ ኦፊሰር ቢያትሪስ ኢጉሉ ገለጹ።

በፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ (POA)፣ በቻይና የአፍሪካ ኅብረት ተልዕኮ እና የውይይት፣ የጥናትና የትብብር ማዕከል ትብብር የተዘጋጀው የቻይና አፍሪካ ስትራቴጂክ የትብብር ዓውደ ጥናት መድረክ በአዲስ አበባ ተካሂዷል።


በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የግብርና፣ ገጠር ልማት ብሉ ኢኮኖሚና ዘላቂ ልማት ዲፓርትመንት ፖሊሲ ኦፊሰር ቢያትሪስ ኢጉሉ እንዳሉት፤ ቻይና በአፍሪካ ያላት ኢንቨስትመንት ለበርካታ አፍሪካውያን ዜጎች የስራ ዕድል ፈጥሯል፡፡

በኢንቨስትመንቱ ከስራ ዕድል ባለፈ ቻይናዊያን ባለሙያዎች ለአፍሪካዊያን እውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዕድል እየፈጠሩ መምጣታቸውን ጠቅሰዋል፡፡

በቻይናና አፍሪካ ግብርና ትብብር ማዕቀፍ የስልጠና መርሃ ግብር 10 ሺህ አፍሪካዊያን ባለሙያዎች በግብርና ሜካናይዜሽን፣ መስኖ ልማት፣ ግብርና ማቀነባበር ላይ የተሰማሩ ኢንዱስትሪ ፓርክ አስተዳደር ላይ ስልጠና መሰጠቱን ለአብነት ጠቅሰዋል፡፡

በብሉ ኢኮኖሚ መስክም ዘላቂ ዓሳ ሀብት ልማት ፣የውሃ ዳርቻዎች መሰረተ ልማት እና በውሃ ሀብት ልማት ላይ የአፍሪካ እና ቻይና ትብብር ከፍተኛ መሆኑንም ተናግረዋል።

ቻይናና አፍሪካ በሃይል እና ኢንዱስትሪ ልማት ላይም ያላቸው አጋርነት ሰፊ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

እንደ ቢያትሪስ ገለጻ፤ እነዚህ የትብብር መስኮች በቻይና እና አፍሪካ መካከል የሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ትብብር እንዲጠናከር እያደረጉ ነው፡፡

በዩኔስኮ ዓለም አቀፍ አቅም ግንባታ ለአፍሪካ ተቋም ዳይሬክተር ክዌንቲን ዎዶን በበኩላቸው፤ በአፍሪካ ያሉ ኢንዱስትሪዎች የሰለጠነ የሰው ሃይል አቅርቦት እጥረት አሁንም ችግር እንደሚያጋጥም ተናግረዋል፡፡

ለዚህ ደግሞ ምክንያቱ በአፍሪካ በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ በሚጠበቀው ደረጃ ስልጠናዎች ማካሄድ ላይ ባለመሰራቱ መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይም ከሰሃራ በታች ባሉ አፍሪካ አገራት የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ቁጥር ዝቅተኛ ነው ያሉት ዳይሬክተሩ፤ በዚህ ዙሪያ ይበልጥ መስራት እንደሚገባ አመላካች ነው ብለዋል፡፡

ወደ ቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የሚገቡ ሰልጣኞች ቁጥር እንዲጨምር ማድረግ፣ በመስኩ የማበረታቻ አሰራሮችን በመዘርጋት የዘርፉን እምቅ አቅም በተሻለ መልኩ ለመጠቀም መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኞችን አቅም መገንባት፣ ለአሰልጣኞች ሳቢ የሆኑ አሰራሮችን መዘርጋት እንደሚገባ አመልክተው፤ ዘመኑ የደረሰበትን የስልጠና ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።

በቻይና ቤጂንግጓ ኖርማል ዩኒቨርስቲ የኤጁኬሸናል ቴክኖሎጂ ትምህርት ክፍል ዲን ማ ኒንግ (ፕ/ር) በበኩላቸው፤ በቻይና ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ የሰው ሰራሽ አስተውሎት (ኤ አይ) በሰፊው ጥቅም ላይ መዋሉን ገልጸዋል። ይህም የትምህርት ጥራቱ ላይ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል።

ሰው ሰራሽ አስተውሎት ለጥናት ምርምርና ፈጠራ በግብዓትነት እያገለገለ መሆኑን ጠቁመው፤ በዚህም ተጠቃሽ ውጤቶች እየተገኙ ነው ብለዋል፡፡

ቻይና እና አፍሪካ በትምህርት እና ስልጠና ዘርፍ ያላቸው ግንኙነት የበለጠ እየተጠናከረ እንደሚሄድ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026