🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥር 14/2018(ኢዜአ)፦ አዲስ አበባ ከተማ እያስመዘገበች የምትገኘው ሁለንተናዊ ለውጥ ለአፍሪካ ከተሞች ተምሳሌት የሚሆን ነው ሲሉ የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ከተሞች ከንቲባዎች ገለጹ፡፡
በአዲስ አበባ የልማትና የገቢ አሰባሰብ እንቅስቃሴ ላይ ያላቸውን አድናቆትም ተናግረዋል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ ሲካሄድ የቆየው የአሕጉራዊ የተሞክሮ ልውውጥ እና የድርጊት መርሃ-ግብር ግምገማ አውደ ጥናት ተጠናቅቋል።
በአውደ ጥናቱ ላይ የተሳተፉ የአፍሪካ ከተሞች ከንቲባዎችና የስራ ኃላፊዎች በአዲስ አበባ ያለውን የልማት እንቅስቃሴና የዲጂታል የገቢ አሰባሰብ ስርዓት ተመልክተዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ከተሞች ከንቲባዎች ጋር በመሆን የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮን የስራ እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል።
በተጨማሪም የአፍሪካ ሀገራት ከተሞች ከንቲባዎች የከተማዋን የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክቶች ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
ተሳታፊዎቹ በጉብኝታቸው ወቅት በአዲስ አበባ የታዘቧቸው ተሞክሮዎች ለሀገሮቻቸው ትልቅ ትምህርት የሚሰጡ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የታንዛንያ ዳሬሰላም ከተማ ከንቲባ ኑረዲን ቢላለ፤ አዲስ አበባ ከተማ ራሷን በራሷ ለማስተዳደር የምታደርገውን ጥረት አድንቀው፤ ስለ አዲስ አበባ ከተማ አሁን በቂ ግንዛቤ አግኝቻለሁ ብለዋል።
ከተማዋ ግብር የምትሰበስብበትንና ተግባራትን የምታከናውንበትን መንገድ መመልከታቸውን ጠቅሰው ከዚህም ሰፊ ልምድ ማግኘታቸውን ተናግረዋል፡፡
ያገኙትን ተሞክሮዎች በዳሬሰላም ተግባራዊ እንደሚያደርጉም ጠቁመዋል፡፡

የሉሳካ ከንቲባ ቺላንዶ ቺታንጋላ አንዲት ከተማ ስኬታማ ለመሆን ጠንካራ የገቢ አሰባሰብ ስርዓት ሊኖራት እንደሚገባ ጠቅሰው፤ በአዲስ አበባ ያየነው የገቢ አሰባሰብ ስርዓትና ገቢ እንዳይባክን የሚደረጉ የፈጠራ ስራዎች የሚደነቁ ናቸው ከዚህም ብዙ ልምድ ቀስመናል ብለዋል።

የካሜሩን ያወንዴ ከተማ የበጀት ቢሮ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አሞዉጎ ብረቲንደ በበኩላቸው፤ በአዲስ አበባ የተመለከቱት የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ድንቅ ነው ሲሉ ገልጸውታል።
በተለይም በገቢ አሰባሰብ በኩል የተመለከቱት የቴክኖሎጂ አጠቃቀም በካሜሩን ሊተገበር የሚገባው ነው ብለዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...
Sep 14, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026