የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በደቡብ ኦሞ ዞን የሚገኙ እምቅ ሃብቶችን በሳይንሳዊ ጥናትና ምርምር በማገዝ የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ መስራት ይገባል

Mar 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ዲመካ፤ የካቲት 21/2018(ኢዜአ)፡- በደቡብ ኦሞ ዞን የሚገኙ እምቅ ሃብቶችን በሳይንሳዊ ጥናትና ምርምር በማገዝ የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ መስራት እንደሚገባ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ተናገሩ።

የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ እና የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አገኘሁ ተሻገር፤ በደቡብ ኦሞ ዞን ዲመካ ከተማ በጂንካ ዩኒቨርሲቲ ለሚገነባው የአርብቶ እና ከፊል አርብቶ አደር የምርምር ኢንስቲትዩት የመሰረተ ድንጋይ አኑረዋል።

ዩኒቨርሲቲው የማዕከሉን ግንባታ በአጭር ጊዜ ውስጥ በማጠናቀቅ የምርምር ስራውን መጀመር ይጠበቅበታል ያሉት አፈ ጉባኤው ሀገር በቀል ዕውቀቶችን በመጠቀም በየአካባቢው ያሉ እምቅ ሀብቶችን በሳይንሳዊ ምርምር በማስደገፍ የላቀ ጥቅም እንዲሰጡ ማድረግ ይገባል ብለዋል።

የምርምር ማዕከሉ የዩኒቨርሲቲው ተመራማሪዎች ብቻ የሚጠቀሙበት ሳይሆን በሀገር ውስጥ እና በተለያዩ የዓለም ሀገራት የሚገኙ ተመራማሪዎች የሚሳተፉበትና ልምድ የሚለዋወጡበት እንደሚሆን ገልጸዋል።

የምርምር ማዕከሉ በተያዘለት ጊዜ በጥራትና በፍጥነት ተጠናቆ ለሚፈለገው ዓላማ እንዲውል አስፈላጊው እገዛ ድጋፍና ክትትል የሚደረግ ይሆናል ብለዋል።

የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዮሐንስ ይትባረክ (ዶ/ር)፤ የሚገነባው የምርምር ማእከል በዋነኝነት አራት መሰረታዊ ተልዕኮዎችን ለመፈፀም የሚያስችል ይሆናል ሲሉ አስረድተዋል።

በአካባቢው የግብርና ሥራ እና የእንስሳት ሀብት በሳይንሳዊ የጥናትና ምርምር በማሳደግ የአርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት ማሳደግ አንዱ ሲሆን የቱሪዝም ሀብትን በምርምር በማገዝ ዓለም አቀፋዊ እውቅና እንዲያገኝ ማድረግም ሌላው መሆኑን አንስተዋል።

በአካባቢው ያሉ ሀገር በቀል ዕውቀቶችን የመሰነድ፣ የማስተዋወቅ እና የማሳደግ ተልእኮን ለማሳካትም ወሳኝ ሚና ይኖረዋል ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026