የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ኢትዮጵያ ውጤታማ የሃይድሮ ዲፕሎማሲ ስራዎችን አከናውናለች 

Mar 25, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 15/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በውሃ ሀብት ረገድ ያላትን የጋራ የመልማት እሳቤና እውነታ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማሳወቅ ውጤታማ የሃይድሮ ዲፕሎማሲ ስራዎች መከናወናቸውን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ገለጹ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ጋር በመተባበር ''ሃይድሮ ዲፕሎማሲና ቀጣናዊ ትብብር ለዘላቂ ውኃና ኢነርጂ ልማትና አስተዳደር'' በሚል መሪ ሃሳብ ቀጣናዊ ጉባኤ በቢሾፍቱ ከተማ ተካሂዷል።


የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) በጉባኤው ላይ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በውሃ ሀብት ላይ ያላትን የጋራ የመልማት እሳቤና ተግባራዊ እንቅስቃሴዎች በተመለከተ ቀደም ሲል ለዓለም በማሳወቅ ረገድ ክፍተቶች ነበሩ።

ይህንን ለማቃለል ባለፉት አራት ዓመታት ደካማ ጎኖችን የመለየትና ሳይንሳዊ ትንታኔዎችን የማዘጋጀት ስራ መከናወኑን ጠቅሰው፤ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በመተባበር በተለይም በዓባይና በታላቁ የህዳሴ ግድብ ላይ ያተኮሩ በርካታ የምርምር ስራዎች ለዓለም እንዲታወቁ መደረጉን ተናግረዋል፡፡

በመረጃ ላይ የተመሰረተ የዲፕሎማሲ ስራ በመሰራቱ ሌሎች ሀገራት ከኢትዮጵያ ጎን ቆመው እውነታውን እንዲረዱ ዕድል መፍጠሩንም ጠቁመዋል፡፡

ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በምታደርገው ጥረት ውሃ ዋነኛው የጀርባ አጥንት መሆኑን ጠቅሰው፤ ለዚህም የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች ተጠናክረው እየተሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።

በጉባኤው ላይ የታደሙት የጎረቤት ሀገራት ሚኒስትሮችም የቀጣናዊ ትብብርን አስፈላጊነት በአጽንኦት ገልጸዋል።


የደቡብ ሱዳን የውኃና መስኖ ሚኒስትር ጀምስ ማዊች፤ የአየር ንብረት ለውጥና የኢነርጂ ፍላጎት መጨመር በውሃ ሀብት ላይ ጫና እያሳደረ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

የድንበር ተሻጋሪ ወንዞችን ፍትሕዊ የጋራ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ያስፈልጋል ያሉት ሚኒስትሩ፤ ለዚህም ደቡብ ሱዳን ለዘላቂ ቀጣናዊ ውሃ ሃብት አጠቃቀም ትብብር ቁርጠኛ ናት ብለዋል።


የዑጋንዳ የውሃና አካባቢ ጥበቃ ሚኒስትር ዴኤታ ቢያትሪስ አቲም፤ የዓባይ ተፋሰስ ሀገራት ከፉክክር ይልቅ ለትብብር ቅድሚያ መስጠት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

በትብብር ላይ የተመሰረተ ቀጣናዊ ብልፅግናን ማረጋገጥ የሁሉንም ህዝቦች ተጠቃሚነት እንደሚያረጋግጥም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026