የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በኢትዮጵያ እና በጣሊያን መካከል ያለውን የኢንቨስትመንት ፍሰት ወደ አዲስ ምዕራፍ አሸጋግሯል 

Mar 26, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ በኢትዮጵያ እና ጣሊያን መካከል ያለውን የኢንቨስትመንት ፍሰት በዓይነትና በመጠን ከፍተኛ ዕድገት እንዲመዘገብ ማስቻሉን የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ገለጹ።

የመጀመሪያው የኢትዮ-ጣሊያን የኮንስትራክሽን፣ የመሰረተ ልማትና የከተማ ልማት ፎረም በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው፡፡


በወቅቱ ንግግር ያደረጉት የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ፤ ኢትዮጵያ ተግባራዊ እያደረገች ያለችው ሁሉን አቀፍ ሪፎርም ለዓለም አቀፍ ኢንቨስትመንት ምቹና ሳቢ ምህዳር ፈጥሯል ብለዋል።

ይህ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ በኢትዮጵያ እና በጣሊያን መካከል ያለውን የኢንቨስትመንት ትስስር በተለያዩ ዘርፎች በዓይነትም ሆነ በመጠን በከፍተኛ ሁኔታ እንዲያድግ ማድረጉን አብራርተዋል።

የጣሊያን ባለሀብቶች በኢትዮጵያ በኮንስትራክሽን፣ በማሽነሪ አቅርቦትና በሌሎች ልዩ ልዩ የኢንቨስትመንት መስኮች በመሰማራት ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገቡ መሆኑን ጠቁመዋል።

የተጀመረው ፎረምም በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች የሚሰማሩ የጣሊያን ባለሀብቶችን ቁጥር ይበልጥ እንደሚያሳድገው ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።

ይህ የሁለቱን ሀገራት ትብብር ከኢኮኖሚ ባለፈ በልማትና በሌሎችም ዘርፎች ይበልጥ የሚያጠናክር መሆኑንም ጠቅሰዋል።

ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎችን የሚስብ የመሰረተ ልማትና የአሰራር ስርዓት እየገነባች መሆኑን ጠቅሰው በተለይም አዲስ አበባ በውጭ ኢንቨስተሮች ዘንድ ተመራጭ መዳረሻ እየሆነች መምጣቷን ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ በርካታ የህዝብ ቁጥር ያላት፣ ምቹ የገበያ ዕድልና መንግስታዊ ክትትል የማይለየው ቀልጣፋ አገልግሎት የሚሰጥባት ሀገር በመሆኗ፣ የቀጣናው መሪ የኢንቨስትመንት መዳረሻነቷን አጠናክራ መቀጠሏን አስረድተዋል።

እንዲሁም ኢትዮጵያ የቀጣናው የልማት፣ የሰላምና የደህንነት ማዕከል ሆና እንደምትቀጥልና የሁለቱ ሀገራት ዘላቂ ትብብርም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።


በኢትዮጵያ የጣሊያን አምባሳደር ሴም ፋብሪዚ በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ እና ጣሊያን የታሪካዊና የረጅም ጊዜ ትብብር ባለቤቶች መሆናቸውን አስታውሰዋል።

ሁለቱ ሀገራት በተለያዩ ዘርፎች የጋራ ራዕይ እንዳላቸው ጠቁመው፤ ይህ ፎረም ትብብራቸውን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ገልጸዋል።

በአዲስ አበባ የታየው የመሰረተ ልማት ዕድገት የሚደነቅ መሆኑን ጠቅሰው ይህንንም ተዘዋውረው መመልከታቸውን አክለዋል፡፡

ለከተማዋ ሁሉን አቀፍ ዕድገት ጣሊያን የበኩሏን ሚና እየተወጣች መሆኑንና በቀጣይም ትብብሩን ለማጠናከር በትጋት እንደምትሰራ አረጋግጠዋል።

በፎረሙ መክፈቻ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር)፣ የጣሊያን የውጭ ጉዳይና ዓለም አቀፍ ትብብር ምክትል ሚኒስትር ማሪያ ትሪፖዲ፣ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ የትምጌታ አስራት(ዶ/ር)፣ በኢትዮጵያ የጣሊያን አምባሳደር ሴም ፋብሪዚ እና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026