🔇Unmute
አምቦ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን በ220 የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች በሚቀጥለው ክረምት የሚተከል የቡና ችግኝ መዘጋጀቱን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።
የጽሕፈት ቤቱ የቡና፣ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ቡድን መሪ አቶ ቶሎሳ አራርሳ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ አርሶ አደሩን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በቡናና ፍራፍሬ ልማት በማሳተፍ ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥ እየተሠራ ይገኛል።
ለዚህም በመጪው ክረምት 5 ነጥብ 7 ሚሊዮን የቡና ችግኝ ለማዘጋጀት ታቅዶ፣ እስካሁን 5 ነጥብ 3 ሚሊዮን ችግኞች ተዘጋጅተዋል።
እንደ ቡድን መሪው ገለጻ፤ ችግኞቹ ከጅማ ግብርና ምርምር ማዕከል የተገኙ የተሻሻሉ ዝርያዎች ሲሆኑ፣ በሽታን የመቋቋም አቅም ያላቸውና በሦስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ምርት መስጠት የሚጀምሩ ናቸው።
የችግኝ ዝግጅቱ በ220 የመንግሥትና የግል የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች እየተከናወነ ሲሆን፣ በሥራው ላይ 16 ሺህ 415 አርሶ አደሮች መሳተፋቸውን ገልጸዋል።
የተዘጋጀው የቡና ችግኝ ሲተከል አንድ ሺህ ሄክታር ገደማ አዲስ መሬት በቡና መሸፈን እንደሚያስችልም ጠቅሰዋል።
ከአዲስ ተከላው በተጓዳኝ ያረጁና ከምርት ውጭ የሆኑ የቡና ዛፎችን የማደስ ሥራም እየተከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026