🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 28/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ምርታማነት ስኬት የተኪ ምርት አቅምን በማጎልበት የወጪ ንግድ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን እያሳደገ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ገለጸ።
በሀገራዊ ለውጡ ማግስት ተቀርፀው ወደ ተግባር የተቀየሩ የብዝሃ-ኢኮኖሚ ስትራቴጂዎች ዛሬ ላይ በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝምና ቴክኖሎጂ ዘርፎች ተጨባጭ ውጤት አስገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄና ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያም የኢንዱስትሪ ዘርፍ መዋቅራዊ የድጋፍና ክትትል ሥርዓት በማጎልበት በወጪ ንግድና ተኪ ምርት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን እያረጋገጠ ነው።
በኢንዱስትሪ ዘርፍ የተመዘገበው እመርታም በኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ዕድገት ጉልህ ድርሻ የሚያበረክትበትን ወሳኝ ዕድል በመፍጠር እያገለገለ ይገኛል።
የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ ታረቀኝ ቡልልታ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በሀገራዊ ለውጡ ማግስት የኢንዱስትሪ ምርታማነትን የሚያበረታታ አስቻይ የፖሊሲ እርምጃ ተወስዷል።

የኢንዱስትሪ ዘርፍ ስትራቴጂክ የፖሊሲ እረምጃው የአምራቾችን የመሠረተ ልማት፣ የኃይልና የፋይናንስ አቅርቦት ማነቆዎችን በቅንጅታዊ የአሰራር ሥርዓት መፍትሔ መስጠት እንዳስቻለ ተናግረዋል።
በተጨማሪም የሀገር ውስጥና የውጭ የኢንዱስትሪ ዘርፍ የኢንቨስትመንት አልሚዎችን ፍሰት በማሳደግ በሀገር የኢኮኖሚ ዕድገት ላይ ገንቢ ሚና የሚወጣበትን ወሳኝ ዕድል መፍጠሩን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ታምርት ሀገር አቀፍ ንቅናቄም ዝቅተኛ የኢንዱስትሪ የማምረት ታሪክ በመቀየር በዘርፉ ላይ እመርታዊ መነቃቃት መፍጠሩን አንስተዋል።
ይህም ኢትዮጵያን የዓለም አቀፍ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት የስበት ማዕከል እንድትሆን እያደረጋት ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያም ሌላኛው ለአምራች ኢንዱስትሪ ምርታማነት አቅም የፈጠረ ወሳኝ ዕድል መሆኑን ገልጸዋል።
ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ እሳቤውም የኢንዱስትሪ ምርታማነትን በማሳለጥ አስቻይ የተኪና ወጪ ንግድ አቅም እንዲፈጠር ማድረጉን አስረድተዋል።
የኢትዮጵያ የመጀመሪያ ካፒታል ገበያ ሥርዓት ለአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ከፍተኛ ፋይዳ እያበረከተ መሆኑን አብራርተዋል።
የካፒታል ገበያም የአምራች ኢንዱስትሪ የፋይናን አቅርቦት ፍላጎትን ምላሽ መስጠት የሚያስችል አማራጭና የረጅም ጊዜ ቁጠባን የሚያበረታታ አስቻይ የአሰራር ምኅዳር እንደፈጠረ አንስተዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026