🔇Unmute
ደሴ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦ለትንሳኤ በዓል የምርት አቅርቦትና የገበያ አማራጮችን በማስፋት የተረጋጋ ግብይት እንዲኖር የተቀናጀ ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑን የደሴ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ አስታወቀ።
በዓሉን ምክንያት በማድረግም በተለያዩ አካባቢዎች በርከት ያሉ ጊዜያዊ የገበያ ስፍራዎች ተከፍተው አገልግሎት በመስጠት ላይ መሆናቸው ታውቋል።

የበዓል ገበያ አቅርቦት፣ ቁጥጥርና አጠቃላይ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ ኢዜአ የደሴ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ ዮናስ እንዳለ ጋር ቆይታ አድርጓል።
ኃላፊውም በማብራሪያቸው በከተማዋ እና አካባቢው የተለያዩ የግብርና እና ኢንዱስትሪ ምርቶች እንዲሁም የእርድ እንስሳት በብዛት እየቀረቡ መሆኑን ገልጸዋል።
የግብርና፣ የኢንዱስትሪ፣ እንስሳትና የእንስሳት ተዋፅኦ ምርቶችን ጭምር በብዛትና በጥራት ለማቅረብ ቀደም ተብሎ ዝግጅት መደረጉን አንስተው በዚህም መሰረት የምርት አቅርቦትና የገበያ አማራጮችን በማስፋት የተረጋጋ ግብይት እንዲኖር ማድረግ ተችሏል ብለዋል።
በግብይት ወቅት ህገ ወጥ ተግባር የሚፈፅሙ ነጋደዎች ሲያጋጥሙም ህብረተሰቡ ለሚመለከታቸው አካላት ወይንም የጸጥታ አካላት መረጃ መስጠት እንዳለበት አስገንዝበዋል።

ለበዓል ሲገበያዩ ካገኘናቸው የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል ወይዘሮ መሰረት ተስፋዬ እና አቶ ዳዊት አራጌ፤ ለበዓል የምርት አቅርቦትና ተደራሽነቱ መልካም ቢሆንም በተለይም በሸቀጦች ላይ መጠነኛ ጭማሬ ስለመኖሩ ገልጸዋል።
በመሆኑም በተቋቋሙት ጊዜያዊ የገበያ ማእከላት ምርቶችን በተሻለ ዋጋ በማግኘታቸው መሸመታቸውን ተናግረዋል።

በተጨማሪም ዘይት፣ ስኳር፣ የዳቦ ዱቄትና ሌሎች የኢንዱስትሪ ውጤት የሆኑ ምርቶችም በሸማቾች ህብረት ስራ ማህብራት በኩል መቅረባቸውን ገልጸዋል።
ለበአል በየአካባቢው ጊዜያዊ የገበያ ማእከላት መቋቋማቸው በአማራጭነት ከመግዛት ባለፈ በቅርበት መሸመት የሚያስችሉ በመሆናቸው መልካም ጅምር መሆኑን ሸማቾቹ ተናግረዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026