🔇Unmute
ደሴ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦ለትንሳኤ በዓል የምርት አቅርቦትና የገበያ አማራጮችን በማስፋት የተረጋጋ ግብይት እንዲኖር የተቀናጀ ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑን የደሴ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ አስታወቀ።
በዓሉን ምክንያት በማድረግም በተለያዩ አካባቢዎች በርከት ያሉ ጊዜያዊ የገበያ ስፍራዎች ተከፍተው አገልግሎት በመስጠት ላይ መሆናቸው ታውቋል።

የበዓል ገበያ አቅርቦት፣ ቁጥጥርና አጠቃላይ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ ኢዜአ የደሴ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ ዮናስ እንዳለ ጋር ቆይታ አድርጓል።
ኃላፊውም በማብራሪያቸው በከተማዋ እና አካባቢው የተለያዩ የግብርና እና ኢንዱስትሪ ምርቶች እንዲሁም የእርድ እንስሳት በብዛት እየቀረቡ መሆኑን ገልጸዋል።
የግብርና፣ የኢንዱስትሪ፣ እንስሳትና የእንስሳት ተዋፅኦ ምርቶችን ጭምር በብዛትና በጥራት ለማቅረብ ቀደም ተብሎ ዝግጅት መደረጉን አንስተው በዚህም መሰረት የምርት አቅርቦትና የገበያ አማራጮችን በማስፋት የተረጋጋ ግብይት እንዲኖር ማድረግ ተችሏል ብለዋል።
በግብይት ወቅት ህገ ወጥ ተግባር የሚፈፅሙ ነጋደዎች ሲያጋጥሙም ህብረተሰቡ ለሚመለከታቸው አካላት ወይንም የጸጥታ አካላት መረጃ መስጠት እንዳለበት አስገንዝበዋል።

ለበዓል ሲገበያዩ ካገኘናቸው የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል ወይዘሮ መሰረት ተስፋዬ እና አቶ ዳዊት አራጌ፤ ለበዓል የምርት አቅርቦትና ተደራሽነቱ መልካም ቢሆንም በተለይም በሸቀጦች ላይ መጠነኛ ጭማሬ ስለመኖሩ ገልጸዋል።
በመሆኑም በተቋቋሙት ጊዜያዊ የገበያ ማእከላት ምርቶችን በተሻለ ዋጋ በማግኘታቸው መሸመታቸውን ተናግረዋል።

በተጨማሪም ዘይት፣ ስኳር፣ የዳቦ ዱቄትና ሌሎች የኢንዱስትሪ ውጤት የሆኑ ምርቶችም በሸማቾች ህብረት ስራ ማህብራት በኩል መቅረባቸውን ገልጸዋል።
ለበአል በየአካባቢው ጊዜያዊ የገበያ ማእከላት መቋቋማቸው በአማራጭነት ከመግዛት ባለፈ በቅርበት መሸመት የሚያስችሉ በመሆናቸው መልካም ጅምር መሆኑን ሸማቾቹ ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...
Sep 14, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026