የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የነዳጅ አቅርቦት እጥረትን ለመቋቋም የተወሰደው የመፍትሄ አቅጣጫ ተግባራዊነቱ እንደቀጠለ ነው

Apr 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደሴ ፤ ሚያዝያ 1/2018 (ኢዜአ)፦ የነዳጅ አቅርቦት እጥረትን ለመቋቋም የተወሰደው የመፍትሄ አቅጣጫ በተቀናጀ መልኩ ተግባራዊነቱ እንደቀጠለ መሆኑን የደሴ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ አስታወቀ።

በመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት ምክንያት የተከሰተውን የነዳጅ አቅርቦት ችግር ለመቋቋም በመንግስት በኩል ግብረ ሃይል ተቋቁሞ የተለያዩ የመፍትሄ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑ ይታወቃል።

የነዳጅን አጠቃቀምን በቁጠባ ማድረግ፣ የታዳሽ ኃይል አማራጮችን የመጠቀም ልምድ፣ የእግር ጉዞ ባህልን ማጎልበት፣ የሕዝብ ትራንስፖርትን መጠቀም፣ በነዳጅ ግብይት ላይ የሚስተዋሉ ሕገ-ወጥ ተግባራትን መቆጣጠር ትኩረት የተደረገባቸው ጉዳዮች ሆነዋል።

በደሴ ከተማ እና አካባቢው ያለውን የነዳጅ አጠቃቀምና አጠቃላይ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን አተገባበር በተመለከተ ኢዜአ የደሴ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ዮናስ እንዳለ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ኃላፊውም በማብራሪያቸው የነዳጅ አቅርቦት እጥረትን ለመቋቋም የተወሰደው የመፍትሄ አቅጣጫ በተቀናጀ መልኩ ተግባራዊነቱ እንደቀጠለ መሆኑን ገልጸዋል።

የእስካሁኑ ሂደት በብዙ መልኩ ሲታይ ውጤታማ እንደነበር አስታውሰው ችግሩ በዘላቂነት እስከሚፈታ ድረስ ለመፍትሄው በጋራ መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል።

የከተማ አስተዳደሩ ግብረ ሃይል በማቋቋም ቅድሚያ ለሚሰጠው በመስጠትና ሌሎች መንግስት ያስቀመጣቸውን አቅጣጫዎች ተግባራዊ ማድረግ መቻሉን አስታወሰው ይህም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ተናግረዋል።

ህብረተሰቡም ችግሩ አለም አቀፍ መሆኑን በመገንዘብ በእግሩ በመጓዝ፣ ጉዞዎችን በመቀነስ፣ በመተባበርና በመረዳዳት ያሳየው መልካም ተግባር የከፋ ችግር እንዳይፈጠር አስችሏል ብለዋል።

በደሴ ከተማ የህዝብ ትራንስፖርት አሽከርካሪ የሆነው ወጣት ሰይድ ይመር፤ የምናገኘውን ነዳጅ በአግባቡ በመጠቀም የህዝብ አገልግሎት እየሰጠን እንገኛለን፤ አጠናክረንም እንቀጥላለን ብሏል።

ሌላኛው የከተማዋ ነዋሪ አቶ ታደሰ ኪዳነማሪያም፤ የነዳጅ አቅርቦት ችግሩ ፈታኝ ቢሆንም ለቀጣይ ብዙ የሚያስተምረን ነገር አለ ብለዋል።

የነዳጅ አቅርቦት ችግሩን ተቋቁሞ ለማለፍ በመንግስት የተቀመጡ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን አድንቀዋል።

በተለይም የነዳጅ ጥገኝነትን በመቀነስ አማራጭ መንገዶችን ማብዛትና የኤሌክትሪክ ሃይል ልማትን ማስፋት ተገቢ መሆኑን አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026