🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና በግብርና ሚኒስቴር ትብብር "ከተረጅነት ወደ ምርታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ በአዳማ ከተማ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
በመድረኩም የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ እውነቴ አለነ፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሰማ ጥሩነህ (ዶ/ር)፣ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) እና የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ (ዶ/ር) ተገኝተዋል።

በተጨማሪም የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሰይፈ ደርቤ፣ የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ ጌቱ ገመቹ ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የፌደራልና የክልል ግብርና ቢሮ የሥራ ኃላፊዎችና የግብርና ሙያተኞች ተገኝተዋል።
በመድረኩም የኢትዮጵያን የግብርና ምርታማነት በማስቀጠል የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የሚያስችሉ የመነሻ ሃሳቦች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል ተብሎ ይጠበቃል።
ኢትዮጵያ በበጋ መስኖ ስንዴ፣ በመኸርና በበልግ ወራት የሰብል ምርታማነት፣በሌማት ትሩፋት እና በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የሚያስችል እመርታዊ ውጤት በማስመዝገብ ላይ ትገኛለች።

ለአብነትም የዘመናት ተረጅነትን በማስቀረት ከራስ አልፎ ስንዴን ወደ ውጪ በመላክ ወደተሟላ ሀገራዊ ክብር መሸጋገር የሚያስችል የታሪክ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...
Sep 14, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026