የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ከተረጅነት ወደ ምርታማነት ፍኖተ ካርታ ትግበራ ድህነትን በመግታት ረገድ ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ ነው

Apr 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ የተረጅነት ታሪክን ወደ ምርታማነት የማሸጋገር ፍኖተ ካርታ ትግበራ ድህነትን በመግታት ረገድ ውጤት እያስገኘ መሆኑን በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሰማ ጥሩነህ (ዶ/ር) ገለጹ።

በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና በግብርና ሚኒስቴር ትብብር "ከተረጅነት ወደ ምርታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ በአዳማ ከተማ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።


በመድረኩም በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሰማ ጥሩነህ (ዶ/ር)፥ "ከተረጅነት ወደ ምርታማነት ለተሟላ ሀገራዊ ሉዓላዊነትና ክብር" በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ የመነሻ ጽሁፍ አቅርበዋል።

በመነሻ ጽሁፋቸውም፥ ኢትዮጵያ በቀደምት ጀግኖች ሉዓላዊነቷን አስጠብቃ የቆየች ሀገር ናት ብለዋል።

ኢትዮጵያ ሉዓላዊነቷን አስጠብቃ የቆየች ሀገር ብትሆንም ተረጅነትና ልመናን ለማስቀረት የነበረው የታሪክ ስብራት የተሟላ ሉዓላዊነትን ማጎናጸፍ ሳይችል እንደቆየ አስረድተዋል።

በዚህም ከሀገራዊ ለውጡ ማግስት የኢትዮጵያን የተሟላ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ የተወሰዱ የፖሊሲ እርምጃዎች ዜጎችን ክብር እያጎናጸፉ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በአየር ንብረት ለውጥና ተያያዥ ጉዳዮች ኢትዮጵያ በድርቅና ርሃብ አደጋ ፈተናዎችን በመቀልበስ እመርታዊ የምርታማነት ሽግግር መደረጉን ተናግረዋል።

የተረጅነት አስተሳሰብን ማስቀረትም ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ሉዓላዊነትና ክብር የላቀ ትርጉም የሚሰጠው መሆኑን አንስተዋል።

የራስ የምርታማነት አቅም በመፍጠር ለአደጋ የማይበገር ማህበረሰብ መገንባት እየተቻለ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።


ይህም የኢትዮጵያን የተሟላ የሉዓላዊነት ፈተናዎች በመቀልበስ የተፈጠረው የምርታማነት አቅም የሀገርን አይበገሬነት በተግባር ያስመሰከረ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያን የተረጅነት ታሪክ ወደ ምርታማነት ለማሸጋገርም መግባባት፣ ማጥራት፣ ማዘጋጀት፣ ማቀናጀትና ማሸጋገር ፍኖተ ካርታ ትግበራ ድህነትን በመግታት ረገድ ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ መሆኑን አስገንዝበዋል።

የልማታዊ ሴፍቲኔት መርሃ ግብርም በርካታ ዜጎችን ከድህነት በማላቀቅ የትርፍ አምራችነት ሽግግርን እያፋጠነ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

በቀጣይም የብልፅግና ፓርቲ አመራርና አባላት፣የመንግሥት የስራ ኃላፊዎችና ሙያተኞች፣ የልማት አጋሮች፣ መገናኛ ብዙኅንና ህዝቡ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተመዘገበውን ስኬት የማስቀጠልና የማፅናት ኃላፊነታቸውን ማስቀጠል እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026