የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በኢኮኖሚ ዘርፍ በተከናወኑ ስራዎች አበረታች ውጤት ተመዝግቧል

Apr 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ቦንጋ፤ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ባለፉት ዘጠኝ ወራት በኢኮኖሚ ዘርፍ በተከናወኑ ስራዎች አበረታች ውጤት መመዝገቡን የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ገለጸ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመንግስትና የፓርቲ የዘጠኝ ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው።


በመድረኩ የክልሉን መንግስት የስራ እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡት የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ሀላፊ ወሰነች ቶማስ እንደገለፁት፤ በበጀት ዓመቱ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በዋና ዋና የኢኮኖሚ ዘርፎች አበረታች ውጤት ተመዝግቧል፡፡

በተለይም የግብርናውን ዘርፍ በማዘመን ምርታማነትን ለማሳደግ በተሰጠው ትኩረት በ2017/18 ምርት ዘመን በመኽር ወቅት 23 ሚሊዮን ኩንታል የሰብል ምርት መሰብሰቡን አንስተው በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ደግሞ እስካሁን 154 ሺህ 279 ኩንታል ምርት መሰብሰቡን ለአብነት ጠቅሰዋል።

በክልሉ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ በተከናወነው ተግባር በግብርና፣ በአገልግሎትና በኢንዱስትሪ ዘርፎች 5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 93 አዳዲስ ኢንቨስትመንቶች ፈቃድ መሰጠቱንም አመልክተዋል።

በተለያዩ ዘርፎች ለ57 ሺህ ዜጎች የስራ ዕድል መፈጠሩንና ከተቋማት ጋር በመተባበር ከ658 ሚሊዮን ብር በላይ ብድር መመቻቸቱን አንስተዋል።


ባለፉት ዘጠኝ ወራት የተከናወኑ ኢኮኖሚያዊ ተግባራት የመንግስትንና የህዝብን ቅንጅት ያሳዩ መሆናቸውን ያነሱት ደግሞ የመድረኩ ተሳታፊና የክልሉ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አክሊሉ ወልደሚካኤል ናቸው።

ተግባሩን ለማላቅም በቀሪ ጊዜያት የተጀመሩ ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ብለዋል።

የክልሉ ጤና ቢሮ ሀላፊ አቶ ኢብራሂም ተማም በበኩላቸው፤ ከመሠረተ ልማት አንፃር እየተደረጉ ያሉ ጥረቶች መልካም መሆናቸውን ጠቁመው በቀጣይም ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገቡትን ለይቶ ትኩረት በመስጠት የተጀመሩ ስራዎች እንዲጠናከሩ ማድረግ ይገባል ብለዋል።

በመድረኩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፣ በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ፍቅሬ አማንን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች እየተሳተፉ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026