የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ አቭዬሽን ሴኩዩሪቲ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅን አፀደቀ

Apr 22, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 13/2018(ኢዜአ)፦ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 15ኛ መደበኛ ስብሰባ የኢትዮጵያ አቭዬሽን ሴኩዩሪቲ አዋጅን ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ አፅድቋል።

የማሻሻያ አዋጅ ለሁለት አስርት ዓመታት ያህል ስራ ላይ የቆየውን አዋጅ የሚተካ ሲሆን፣ በዘርፉ የታዩ አዳዲስ የደህንነት ስጋቶችንና የቴክኖሎጂ ለውጦችን ግምት ውስጥ ያስገባ መሆኑ ተገልጿል።

በምክር ቤቱ የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈቲህ መሀዲ (ዶ/ር) የረቂቅ አዋጁን ሪፖርትና የውሳኔ ሃሳብ ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።

በገለጻቸውም ነባሩ አዋጅ ከ20 ዓመታት በላይ ያገለገለ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት በአቭዬሽን ኢንዱስትሪው የሚታዩ ውስብስብ የደህንነት ስጋቶችን ለመከላከል አቅሙ ውስን እንደነበረ አስገንዝበዋል።

አዲሱ አዋጅ የአቭዬሽን ዘርፉን ደህንነት ለማስጠበቅ በርካታ ፋይዳዎች እንዳሉት ጠቅሰው ዘመኑ ያመጣቸውንና ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተወሳሰቡ የመጡ ስጋቶችን በብቃት መከላከል የሚያስችል ጠንካራ የሕግ ማዕቀፍ ይፈጥራል ብለዋል፡፡

የአቭዬሽን ደህንነት ፍተሻና የቁጥጥር ሥራዎች ይበልጥ በቴክኖሎጂ የታገዙ፣ ቀልጣፋና አስተማማኝ እንዲሆኑ ያስችላል ያሉት ምክትል ሰብሳቢው የኢትዮጵያን የአቭዬሽን ሴኩዩሪቲ አሠራር ከዓለም አቀፍ የሲቪል አቭዬሽን ድርጅት መለኪያዎችና መስፈርቶች ጋር የተጣጣመ ያደርገዋል ብለዋል።

አዲሱ አዋጅ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕም ሆነ ሌሎች በዘርፉ የተሰማሩ ተቋማት ለዓለም ማህበረሰብ ደህንነቱ የተጠበቀና አስተማማኝ የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጡ ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር ጠቁመዋል።

አየር መንገዱ በዓለም አቀፍ ደረጃ እያሳየ ያለውን ስኬትና የሀገሪቱን መልካም ገጽታ አጠናክሮ ለማስቀጠል ወቅቱን የዋጀ የሕግ ድጋፍ አስፈላጊ መሆኑንም አክለዋል።

የምክር ቤቱ አባላት በአዋጁ ላይ ሰፊ ውይይት ካደረጉ በኋላ፣ አዋጁ የሀገሪቱን ብሔራዊ ደህንነትና ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ያለውን ፋይዳ አድንቀዋል።

ምክር ቤቱ የቀረበለትን የውሳኔ ሃሳብ መርምሮ፣ አዲሱን የኢትዮጵያ አቭዬሽን ሴኩዩሪቲ ማሻሻያ አዋጅ በአብላጫ ድምፅ አፅድቋል።

ይህ የማሻሻያ አዋጅ ለሁለት አስርት ዓመታት ያህል ስራ ላይ የቆየውንና በ1997 ዓ.ም የወጣውን ነባር አዋጅ ቁጥር 432/1997 የሚተካ ሲሆን፣ በዘርፉ የታዩ አዳዲስ የደህንነት ስጋቶችንና የቴክኖሎጂ ለውጦችን ግምት ውስጥ ያስገባ እንደሆነም ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026