የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የተቀናጀ የሚዲያ ሬጉላቶሪ ቴክኖሎጂ የሚዲያ ተቋማት ኃላፊነታቸውን የበለጠ እንዲወጡ ያግዛል

May 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 23/2018(ኢዜአ)፦ የተቀናጀ የሚዲያ ሬጉላቶሪ እና የአስተዳደር ሥርዓት ቴክኖሎጂ፣ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት ሥራቸውን በኃላፊነት ስሜት የበለጠ እንዲያከናውኑ እንደሚያስችል የሥራ ኃላፊዎች ገለጹ።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ከኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ያለማውን የተቀናጀ የሚዲያ ሬጉላቶሪ እና አስተዳደር ሥርዓት ቴክኖሎጂ በይፋ ሥራ አስጀምሯል።


የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሰይፈ ደርቤ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በርካታ ተቋማትን እየደገፈ ይገኛል።

ኢንስቲትዩቱ በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ዕድገት ውስጥ አሻራውን እያሳረፈ እንደሚገኝ ጠቁመው፤ በዛሬው ዕለት ወደ ሥራ የገባው የተቀናጀ የሚዲያ ሬጉላቶሪ እና አስተዳደር ሥርዓት ቴክኖሎጂ ለሚዲያው ዘርፍ ዕድገት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው ብለዋል።

በተለይ ግልጽነትና ፍትሐዊነትን ለማስፈን ትልቅ ዕድል እንደሚፈጥር ገልጸው፤ የሚዲያ ተቋማት ኃላፊነትን በተላበሰ መንገድ ሥራቸውን እንዲያከናውኑ እንደሚያግዝ ተናግረዋል።


የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አድማሱ ዳምጠው፤ የተቀናጀ የሚዲያ ሬጉላቶሪ እና አስተዳደር ሥርዓቱ የማኑዋል አሠራርን የሚያስቀር መሆኑን ገልጸዋል።

እንዲሁም ትክክለኛነትን የሚያረጋግጥና ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚያስችል እንዲሁም ለሚዲያዎች ራሱ እንደ ግብረ መልስ ያገለግላል ብለዋል።


የኤን.ቢ.ሲ ኢትዮጵያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብሩክ ከበደ በበኩላቸው፤ ቴክኖሎጂው የኅብረተሰቡን ተሳትፎ የሚያረጋግጥና ተጠያቂነትን የሚያሰፍን መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይም በመገናኛ ብዙኃን መካከል ያለውን መልካም ግንኙነት እንደሚያጠናክር ተናግረዋል።


የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ ጄይላን አብዲ፤ ቴክኖሎጂው ተጠያቂነት ያለው አሠራርን የሚያረጋግጥ፣ ሥራን የሚያቃል፣ ግልጽነትን የሚፈጥርና የተቋሙን ውጤታማነት የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቁመዋል።


በመርሐ ግብሩ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)፣ የብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራል እና የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ቦርድ ሰብሳቢ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን፣ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትዓለም መለሰ፣ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሃይማኖት ዘለቀ፣ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር)፣ የመገናኛ ብዙኃን የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026