🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 26/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን የቱሪዝም ጸጋዎች በአግባቡ ጥቅም ላይ ለማዋል የግል ዘርፉ በሆቴልና በመዳረሻ ልማት ላይ የሚኖረው ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባሕር ዳር ታሪኳን ሳትለቅ ዘመኑን እየዋጀች መሆኑን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።
ቀደም ሲል የከተማዋ ትዝታ በነበረው በታሪካዊው ጣና ሆቴል ሥፍራ ዓለም አቀፍ ደረጃን ያሟላ የፎር ፖይንትስ ባይ ሸራተን (Four Points by Sheraton) ሆቴል የግንባታ ፕሮጀክት በይፋ መጀመሩን አመልክተዋል።

በሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የሚገነባው ይህ የሆቴል ፕሮጀክት ከተማዋን የቱሪዝም ሠገነት እንደሚያደርጋት ተናግረዋል።
በርካታ አገልግሎቶችን አሟልቶ በአሥራ ስምንት ወራት ግንባታው የሚጠናቀቀው ይህ ሆቴል፣ የግል ባለ ሀብቱ በሀገሪቱ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ውስጥ ያለውን ሚና በተግባር የሚያሳይ ነው ብለዋል።

ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በተለያዩ ዘርፎች እያመጣ ያለው ለውጥ የሚደነቅ መሆኑን የገለጹ ሲሆን፣ ይህ የሆቴል ግንባታም ለባሕር ዳር በጸጋ ላይ ጸጋ የሚጨምር መሆኑንም ነው የተናገሩት።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ፕሮጀክቱን በይፋ ባስጀመሩበት ወቅት ለከተማዋና ለሀገሪቱ ሕዝብ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026