የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

May 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተመላከተ።

የደብረ ማርቆስ ከተማ ገጽታን የሚገነባ፣ ቅርሶቿን በማስተዋወቅ ለትውልድ ለማስተላለፍ የሚያስችል "ሚያዚያን በማርቆስ" የተሰኘ ፌስቲቫል ዛሬ ተካሄዷል።


የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ተሾመ ዋለ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት ፤በከተማዋ የሚገኙ የመስህብ ሃብቶችና ፀጋዎች በማስተዋወቅ ህብረተሰቡን ከዘርፉ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው።

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋል ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኝ ገልጸዋል።


ይህም ቅርሶችና እሴቶች የቀድሞ ይዘታቸውን ጠብቀው ለመጪው ትውልድ እንዲተላለፉ ከማድረግ ባሻገር ጎብኚዎችን ለመሳብ ያስችላል ብለዋል።

ዛሬ የተካሄደው "ሚያዚያን በማርቆስ" የባህል ፌስቲቫል እና ፓናል ውይይት በከተማዋ የሚገኙ የመስህብ ሃብቶችን በመለየትና በማስተዋወቅ የሀብት ምንጭ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑን አስረድተዋል።

የከተማ አስተዳደሩ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ አእምሮ በበኩላቸው እንደገለጹት "ሚያዚያን በማርቆስ" የአካባቢውን ቱባ ባህል ጠብቆ ለተተኪው ትውልድ ለማስተላለፍ የሚያስችል ነው።


ባለፉት አራት ዓመታት ፌስቲቫሉን በማካሄድ የአካባቢውን ማህበረሰብ መስተጋብር በማጠናከርና የአገር ውስጥ ቱሪስቶች ወደ አካባቢው እንዲመጡ በማድረግ ለውጥ ማምጣት ተችሏል ብለዋል።

የተጀመሩ ተግባራትን አጠናክሮ በማስቀጠል ከቱሪዝም ልማቱ የሚገኘውን ዘላቂ ጥቅም ለማስፋት እየተሰራ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

በፌስቲቫሉ የከተማዋና የአካባቢው ማህበረሰብ፣ የባህል አምባሳደሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች መሳተፋቸውም ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026