የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በክልሉ ዲጂታል ኢትዮጵያን ለማሳካት ትምህርት ቤቶችን መሰረት ያደረጉ ሥራዎች ተጀምረዋል

May 12, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር፤ ግንቦት 3/2018 (ኢዜአ)፦በአማራ ክልል ዲጂታል ኢትዮጵያን ለማሳካት ትምህርት ቤቶች ላይ መሰረት ያደረጉ ሥራዎች መጀመራቸውን የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው የተማሪዎችና የትምህርት ቤቶች የሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ስልጠናና ውድድር አካሂዷል።

በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ የውድድሩ አስተባባሪ አቶ ሃብታሙ ላቀ እንደገለጹት ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ትምህርት ቤቶች ላይ ትኩረት በማድረግ እየተሰራ ነው።


ለተግባራዊነቱም ከክልሉ ትምህርት ቢሮ ጋር በመተባበር የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች የሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራን ለማሳደግ ስልጠናዎችና በሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ፕሮጀክት ውድድር በማድረግ ልምድ የሚቀስሙበትን አውድ ለማስፋት መሰራቱን ጠቁመዋል።

የእዚሁ አካል የሆነውና በሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ፕሮጀክት ተወዳድረው ከ1 እስከ 3 በመውጣት የላቀ ውጤት ላስመዘገቡት ተማሪዎች የማበረታቻ ሽልማት መስጠቱንም አስረድተዋል።


ማበረታቻውም ተማሪዎችና ትምህርት ቤቶች በሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ላይ አተኩረው በመስራት የዲጂታል ኢትዮጵያ ግቦችን ለማሳካት የላቀ ተነሳሽነት እንዲኖራቸው ያስችላል ብለዋል።

በቢሮው የኤሌክትሮኒክስ መንግስት አገልግሎት ቡድን መሪና የውድድሩ ዳኛ አቶ ደጀኔ ብርሃኔ በበኩላቸው የተማሪዎችን የቴክኖሎጂ እውቀት በማሳደግ ችግር ፈች ሥራዎችን ለማህበረሰቡ እንዲያቀርቡ መሰራቱን ጠቁመዋል።


ለውድድሩ የቀረቡት ፕሮጀክቶችም የዚሁ ሥራ አካል መሆናቸውን ጠቁመው፣ መመዘኛዎቹ የፈጠራ ጽንሰ ሃሳብ ችግር ፈችነት፣ የፈጠራው አተገባበር ጥራት፣ አረዳድና አቀራረብ ላይ መስረት ያደረጉ መሆናቸውን አስረድተዋል።

ውድድሩ ተማሪዎች በቀጣይ በቴክኖሎጂና በመካኒካል የፈጠራ ሥራዎች የጀመሯቸውን ተግባራት ዳር በማድረስ ለአገር ጥቅም እንዲያውሉና ሌሎች ተማሪዎችም የእነሱን ፈለግ እንዲከተሉ መነሳሳት የፈጠረ ነው ብለዋል።

ከካቶሊክ ትምህርት ቤት የመጣው የ10ኛ ክፍል ተማሪ ቅዱስ አላምረው የግብርናውን ዘርፍ ችግር የሚፈታ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ውጤት በማቅረብ 1ኛ በመውጣት ተሸልሟል።


የፈጠራ ሥራው ለአርሶ አደሩ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችል መሆኑን ገልጾ ይህም የመሬት ለምነት፣ የአየር ጸባይን እና የዝናብ ሁኔታን በመለየት ምን አይነት ሰብል መዘራት እንዳለበት መረጃ የሚሰጥ መሆኑን ነው የገለጸው።

የጣና ሃይቅ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ አብርሃም ዮሴፍ በበኩሉ በውድድሩ “የቤት ጥበቃ ሲስተም” የፈጠራ ስራ በማቅረብ 2ኛ ደረጃን አግኝቶ መሸለሙን ገልጿል።


ፕሮጀክቱም በመኖሪያ ቤት ላይ የሚደርስን በጭስ መታፈን፣ የእሳት አደጋ፣ የስርቆት ወንጀልና ሌሎች አደጋዎችን ለመከላከል የሚያስችል ነው ብሏል።

ከዚህ በተጨማሪ የመኖሪያ ቤትን ሙቀት መጥኖ በመቆጣጠር የነዋሪዎችን ጤንነትና ደህንነት ለመጠበቅ የሚያስችል መሆኑን ጠቁሞ ፕሮጀክቱ በቀላሉ የሚተገበርና አዋጭ መሆኑን ገልጿል።

ለሦስት ቀናት በተካሄደው የስልጠናና የውድድር መድረክ ከሰባት ትምህርት ቤቶች የመጡ ተማሪዎች 19 የፈጠራ ፕሮጀክቶችን ያቀረቡ ሲሆን በውድድሩ ከ1 እስከ 3 ለወጡትም ቢሮው የገንዘብ ሽልማት አበርክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026