የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ኢትዮጵያዊያን ያሸነፉበት የዓለም አቀፉ የታዳጊዎች ሮቦቲክስ ውድድር

May 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ) ፦ የኢትዮጵያ ታዳጊዎች ልዑክ በዓለም አቀፉ የታዳጊዎች የሮቦቲክስና ሰው ሰራሽ አስተውሎት ሻምፒዮና በመሳተፍ በህዝብ ምርጫ ሽልማት ዘርፍ 1ኛ በመሆን አጠናቋል፡፡

በሚቺጋን አሜሪካ ሎውረንስ ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በተካሄደው የ2026 የሮቦፌስት ዓለም አቀፍ የታዳጊዎች የሮቦቲክስና ሰው ሰራሽ አስተውሎት ሻምፒዮና ኢትዮጵያዊያን ተወዳዳሪዎች አስደናቂ ድሎችን አስመዝግበዋል።

ዘንድሮ በተካሄደው ውድድር (Robofest 2026 International Championships) ኢትዮጵያውያን ታዳጊዎች ከ39 የቴክኖሎጂ ሀያላን ሀገራት ከተወጣጡ 738 ቡድኖች ጋር በመፎካከር ነው በተለያዩ ዘርፎች ማሸነፍ የቻሉት፡፡

በውድድሩ በህዝብ ምርጫ ሽልማት ዘርፍ ኢትዮጵያውያን ታዳጊዎች ቀዳሚ በመሆን ሲያሸንፉ፥ በህክምና ሮቦቲክስ ዘርፍ 5ኛ እንዲሁም በፈጠራ ማሳያ 6ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል፡፡

ከአንድ ወር በፊት በግሪክ በተካሄደው ዓለም አቀፍ ሚኖአን ሮቦቲክስ ሻምፒዮና ላይ ኢትዮጵያውያን ታዳጊዎች 2ኛ ደረጃን በማግኘት የሀገራቸውን ስም ማስጠራታቸው የሚታወስ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026