የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በክልሉ በለውጡ ዓመታት የህዝብን የልማት ጥያቄ መሰረት ያደረጉ የተለያዩ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

May 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ወንሾ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በሲዳማ ክልል በለውጡ ዓመታት የህዝብን የልማት ጥያቄ መሰረት ያደረጉ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ስራዎች መከናወናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ።

ርዕሰ መስተዳድሩ በማዕከላዊ ሲዳማ ዞን ወንሾ ወረዳ የተገነቡ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን ዛሬ መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።


በምረቃው ላይ ርዕሰ መስተዳድሩ እንደገለጹት፣ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በክልሉ የህዝብን የልማት ጥያቄ መሰረት ያደረጉ ዘርፈ ብዙ የመሰረተ ልማት ሥራዎች ተከናውነዋል።

በዚህም ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ተጨባጭ ውጤቶች መገኘታቸውን ጠቅሰው፣ በልማት ሥራዎቹ የህብረተሰቡ የተቀናጀ ተሳትፎ ጉልህ መሆኑን ተናግረዋል።


ዛሬ የተመረቁ የልማት ፕሮጀክቶች የክልሉ መንግስትና በየደረጃው ያሉ መዋቅሮች በቅንጅት ያስመዘገቡት ውጤት ነው ብለዋል።

የልማት ፕሮጀክቶቹ የአገልግሎት አሰጣጥን በማሳለጥ የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች የሚፈቱ መሆናቸውንም አስታውቀዋል።

የወንሾ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ወልዴ ዩምራ በበኩላቸው፤ በወረዳው የተገነቡ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ከ700 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸውና ህዝቡም የተሳተፉባቸው ናቸው ብለዋል።


ዛሬ ተመርቀው ለአገልግሎት ከበቁ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶቹ መካከል ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት፣ የወረዳ አስተዳደር ሕንጻ እና ሌሎች አገልግሎት የሚያሳልጡ የመንግስት ተቋማት እንደሚገኙበትም አመልክተዋል።

የአካባቢው ህብረተሰብ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄዎችን በሂደት የመመለስ አቅም እያደገ መምጣቱን ገልጸው፣ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች በቀጣይም ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።

አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ የአካባቢው ነዋሪዎች መካከል አቶ ሽታዬ እሳቱ፤ የለውጡ መንግስት ህብረተሰቡን በማስተባበር ባከናወናቸው የልማት ፕሮጀክቶች ህዝቡ ተጠቃሚነቱ እየተረጋገጠ መጥቷል።

ዛሬ የተመረቁ ፕሮጀክቶችም አገልግሎትን የሚያሳልጡና የወረዳውን እድገት የሚያፋጥኑ ናቸው ብለዋል።


በመርሃ ግብሩ ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንታዬ ከበደ፣ የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ አብርሃም ማርሻሎ እንዲሁም ሌሎች የክልሉና የፌደራል መንግስት የሥራ ሃላፊዎችና የህብረተሰብ ክፍል ተወካዮች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026