የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በክልሉ በለውጡ ዓመታት የህዝብን የልማት ጥያቄ መሰረት ያደረጉ የተለያዩ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

May 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ወንሾ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በሲዳማ ክልል በለውጡ ዓመታት የህዝብን የልማት ጥያቄ መሰረት ያደረጉ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ስራዎች መከናወናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ።

ርዕሰ መስተዳድሩ በማዕከላዊ ሲዳማ ዞን ወንሾ ወረዳ የተገነቡ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን ዛሬ መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።


በምረቃው ላይ ርዕሰ መስተዳድሩ እንደገለጹት፣ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በክልሉ የህዝብን የልማት ጥያቄ መሰረት ያደረጉ ዘርፈ ብዙ የመሰረተ ልማት ሥራዎች ተከናውነዋል።

በዚህም ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ተጨባጭ ውጤቶች መገኘታቸውን ጠቅሰው፣ በልማት ሥራዎቹ የህብረተሰቡ የተቀናጀ ተሳትፎ ጉልህ መሆኑን ተናግረዋል።


ዛሬ የተመረቁ የልማት ፕሮጀክቶች የክልሉ መንግስትና በየደረጃው ያሉ መዋቅሮች በቅንጅት ያስመዘገቡት ውጤት ነው ብለዋል።

የልማት ፕሮጀክቶቹ የአገልግሎት አሰጣጥን በማሳለጥ የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች የሚፈቱ መሆናቸውንም አስታውቀዋል።

የወንሾ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ወልዴ ዩምራ በበኩላቸው፤ በወረዳው የተገነቡ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ከ700 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸውና ህዝቡም የተሳተፉባቸው ናቸው ብለዋል።


ዛሬ ተመርቀው ለአገልግሎት ከበቁ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶቹ መካከል ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት፣ የወረዳ አስተዳደር ሕንጻ እና ሌሎች አገልግሎት የሚያሳልጡ የመንግስት ተቋማት እንደሚገኙበትም አመልክተዋል።

የአካባቢው ህብረተሰብ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄዎችን በሂደት የመመለስ አቅም እያደገ መምጣቱን ገልጸው፣ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች በቀጣይም ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።

አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ የአካባቢው ነዋሪዎች መካከል አቶ ሽታዬ እሳቱ፤ የለውጡ መንግስት ህብረተሰቡን በማስተባበር ባከናወናቸው የልማት ፕሮጀክቶች ህዝቡ ተጠቃሚነቱ እየተረጋገጠ መጥቷል።

ዛሬ የተመረቁ ፕሮጀክቶችም አገልግሎትን የሚያሳልጡና የወረዳውን እድገት የሚያፋጥኑ ናቸው ብለዋል።


በመርሃ ግብሩ ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንታዬ ከበደ፣ የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ አብርሃም ማርሻሎ እንዲሁም ሌሎች የክልሉና የፌደራል መንግስት የሥራ ሃላፊዎችና የህብረተሰብ ክፍል ተወካዮች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026