የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የኃይል አቅርቦትን አስተማማኝነትና ዘላቂነት ለማረጋገጥ የፀሃይ ሃይል ልማትን ለማስፋፋት ትኩረት ተሰጥቷል

Jun 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፡-የኃይል አቅርቦትን አስተማማኝነትና ዘላቂነት ለማረጋገጥ የፀሃይ ሃይል ልማትን ለማስፋፋት ትኩረት መሰጠቱን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ገለፀ።

ሚኒስቴሩ አማራጭ የኃይል ምንጮችን ለማስፋፋትና በዘርፉ የባለድርሻ አካላት ተሳትፎን ለማጠናከር ያለመ የውይይት መድረክ በአዳማ በማካሄድ ላይ ይገኛል ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) እንደገለፁት ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም በታዳሽ ሃይል ልማት ላይ በትኩረት እየሰራች ትገኛለች።

በተለይ በውሃ፣ በፀሃይ፣ በንፋስና በጂኦተርማል ሃይል ልማት ላይ ትኩረት መደረጉን ገልጸው


በአሁኑ ወቅት 96 በመቶ የሚሆነው የሃይል አቅርቦት ከኃይድሮ ኤሌክትሪክ የሚገኝ መሆኑን ገልጸዋል።

እንደ ሚኒስትር ዴኤታው ገለጻ አስተማማኝና ዘላቂ የሃይል አቅርቦትን ለማረጋገጥ አማራጭ የሃይል ልማት የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው ብለዋል።

ከአማራጭ ታዳሽ ሃይል ልማት የፀሃይ ሃይል ልማት አንዱ መሆኑን ጠቅሰው ልማቱ ላይ የግሉን ዘርፍና ባለድርሻ አካላትን ለማሳተፍ የሚያስችሉ የህግ ማዕቀፎችና አሰራሮች መዘርጋታቸውን ገልጸዋል።

በተለይም የፀሀይ ኃይል ልማቱ አርሶና አርብቶ አደሮች በመስኖና በተለያዩ የስራ መስኮች በዘላቂነት እንዲሳተፉና ህይወታቸው እንዲለወጥ በማድረግ ረገድ ቁልፍና አጋዥ መሆኑንም ተናግረዋል።

ከዋና የሃይል መስመር ርቀው የሚገኙ ወረዳዎችና የገጠር ቀበሌዎችን የመብራት ተጠቃሚ ከማድረግ ባለፈ ንፁህ የመጠጥ ውሃ እንዲያገኙ ብሎም በመስኖ ልማት እንዲሳተፉ ጭምር ውጤት እየተገኘበት ነው ብለዋል።


በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የዩ.ኤን.ዲ.ፒ አፍሪካ ሚኒግሪድ ፕሮግራም ማኔጀር አቶ ይመስላል ተፈራ በበኩላቸው የግሉ ዘርፍ በፀሃይ ሃይል ልማት እንዲሳተፍና ዘርፉ በትብብር እንዲለማ ምቹ ሁኔታን መፍጠር ያስፈልጋል ብለዋል።

በተለይ ከህግ ማዕቀፎች ጀምሮ በርካታ የአሰራር ማሻሻያዎች መዘጋጀታቸውን ጠቅሰው የሃይል ዘርፉ አንዱ የኢንቨስትመንት መስክ መሆኑንም ገልጸዋል።

በተለይ በግብርና ዘርፍ ብቻ የተወሰኑ የህብረት ስራ ማህበራትና ዩኒየኖች በጸሃይ ኃይል ልማት በመሳተፍ ገበያ ተኮርና የገቢ አቅማቸውን የሚያሳድግ ሰፋፊ የግብርና መስኖ ልማት እንዲያከናውኑ ዕድልን የሚሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል።

በዚህም ፕሮግራሙ ለህብረት ስራ ማህበራትና ዩኒየኖች በጸሃይ ኃይል ልማት ላይ የአቅም ግንባታ ስልጠና ከመስጠት ባለፈ በፓይለት ደረጃ በሐዋሳ፣ ሶማሌና ቄለም ወለጋ ዞኖች እየሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል።


በኦሮሚያ ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮ የኢነርጂ አቅርቦት ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ሶሬሳ ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ጋር በታዳሽ ሃይል ልማት ማስፋፋት ላይ በትኩረት እየሰራን እንገኛለን ብለዋል።


በተለይ በቄለም ወለጋ ላሎ ቂሌ ወረዳ የሚኒግሪድ የፀሃይ ሃይል ልማት ለማከናወን በትብብር እየተሰራ መሆኑን ገልጸውበተጨማሪም የክልሉ የህብረት ስራ ማህበራትና ዩኒየኖች በፀሃይ ኃይል ልማት እንዲሳተፉ የአቅም ግንባታ ስልጠና እየሰጠ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026