የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን የሐሰተኛ መረጃ እና የጥላቻ ንግግር ለመከላከል የሚያስችል የቴክኖሎጂ አቅሙን እያሳደገ ነው

Jun 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የሐሰተኛ መረጃዎችና የጥላቻ ንግግሮችን ለመከላከል የሚያስችል የቴክኖሎጂ አቅም እያሳደገ መሆኑን ዋና ዳይሬክተሯ ሃይማኖት ዘለቀ ገለጹ።

ትውልዱ በጤናማ አስተሳሰብ ለአገር ዕድገት፣ ልማትና ብልፅግና የራሱን አዎንታዊ አስተዋጽኦ እንዲያደርግ ማስቻል እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሃይማኖት ዘለቀ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ በአሁኑ ወቅት ስማርት ፎን የያዘ እያንዳንዱ ዜጋ የሚሳተፍበት ሰፊ የተግባቦት ዘዴ ተፈጥሯል።

ይህ አዝማሚያ ጥሩ ተሞክሮዎችን ለመለዋወጥና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ትልቅ ዕድል ይዞ የመጣ መሆኑን አመልክተው፤ በሌላ በኩል ግን ሙያዊ ሥነ-ምግባር የሌላቸው በርካታ አካላት የሚሳተፉበት በመሆኑ ትልቅ ፈተና እየደቀነ እንደሚገኝ አብራርተዋል።

አብዛኛው የዲጂታል ሚዲያ ተጠቃሚ የጋዜጠኝነት ሙያዊ ሥልጠና የሌለው በመሆኑ እንደ ትክክለኛነት፣ ሚዛናዊነት እና ታማኝነት ያሉ መሠረታዊ የጋዜጠኝነት ምሰሶዎች አደጋ ላይ መውደቃቸውን ተናግረዋል።

ይህም ኃላፊነት የማይወስዱ፣ ስህተታቸውን ሳያርሙ የሚያሰራጩ የይዘት ፈጣሪዎች መበራከታቸውን ጠቅሰው፤ የሐሰተኛ መረጃዎችና የጥላቻ ንግግሮች ስርጭት እንዲሰፋ ምክንያት መሆኑን አስገንዝበዋል።

ትውልዱ በጤናማ አስተሳሰብ ለአገር ዕድገት፣ ልማትና ብልፅግና የራሱን አዎንታዊ አስተዋጽኦ እንዲያደርግ ማስቻል እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።

የሐሰተኛ መረጃ ስርጭት አገር አጥፊ መሆኑን የጠቀሱት ዋና ዳይሬክተሯ፤ ይህንን የሚጸየፍ ትውልድ ለመፍጠር ሁሉም በጋራና በኃላፊነት ስሜት ሊረባረብ እንደሚገባ ተናግረዋል።

ባለሥልጣኑ እነዚህን ተግዳሮቶች ለመከላከል አሠራሩን ከማኑዋል ወደ ዲጂታል እየቀየረ መሆኑን ገልጸው፤ ከአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ተቋሙን የማዘመን ሥራዎች በስፋት እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም መሠረት የተመዘገቡትንም ሆነ ያልተመዘገቡትን የዲጂታል ሚዲያ ይዘቶች በቴክኖሎጂ ለመከታተል የሚያስችል አሠራር ተዘርግቷል ብለዋል።

በተለይም የሰዎችን ድምፅና ምስል በመቀየርና በማስመሰል ሕዝብን ወደተሳሳተ ውሳኔ የሚመሩ የ"ዲፕ ፌክ" (Deepfake) ቴክኖሎጂዎችን ለመቆጣጠር የሚያስችለውን የመጀመሪያ ምዕራፍ ሥራ አጠናቆ ተቋሙ ወደ ሁለተኛው ምዕራፍ መሸጋገሩን ይፋ አድርገዋል።

በአሁኑ ወቅት ባለሥልጣኑ ፈቃድ የሰጣቸውን 73 የበይነ-መረብ ሚዲያዎችን የቅርብ ክትትልና ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

ወደፊትም ሁሉም የዲጂታል ሚዲያ አካላት ተመዝግበውና ኃላፊነት ወስደው እንዲሠሩ የሚያስገድድ የሕግ ማዕቀፍና የአዋጅ ማሻሻያ ሥራዎች እየተሠሩ መሆኑን አስታውቀዋል።

ከዚህ ቀደም የሐሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግር ጥቆማዎች በ9192 ነጻ የስልክ መስመር ብቻ ይሰበሰቡ እንደነበር ያስታወሱት ዋና ዳይሬክተሯ፤ አሁን ግን "ኤማ አፕ" (Ema App) የተሰኘ አዲስ አፕሊኬሽን በይፋ ሥራ መጀመሩን ተናግረዋል።

ይህ አሠራር በተዘረጋ በጥቂት ቀናት ውስጥ ብቻ ከ47 በላይ ጥቆማዎች በዚሁ መተግበሪያ በኩል መድረሳቸውን ጠቅሰው፤ ሊንክና ስክሪንሹት መኖሩ የመረጃውን ባለቤት በቀላሉ ለማወቅና ተጠያቂነትን ለማስፈን ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

የሐሰተኛ መረጃንና የጥላቻ ንግግርን የመከላከል ሥራ የባለሥልጣኑ ብቻ እንዳልሆነና ወደፊትም ከሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም፣ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን እና ከሌሎች የዴሞክራሲያዊ ተቋማት ጋር ያለውን ትብብር ይበልጥ በማጠናከር እንደሚሠራ አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026