የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በከተማችን የተከናወኑ የሰላምና ልማት ተግባራት ውጤታማና ልምድ የሚወሰድባቸው ናቸው- የወልዲያ ከተማ ነዋሪዎች

Jun 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ወልድያ ፤ሰኔ 7/2018 (ኢዜአ)፡- በከተማችን የተከናወኑ የሰላምና ልማት ተግባራት ውጤታማና ልምድ የሚወሰድባቸው ናቸው ሲሉ የወልዲያ ከተማ ነዋሪዎች ገለፁ።

ነዋሪዎቹ እንደገለፁት፤ ከከተማ አስተዳደሩ ጎን ተሰልፈን የከተማችንን ሰላም በንቃት በመጠበቅ የተጀመሩ አስደናቂ የልማት ስራዎችን አጠናክረን እንቀጥላለን።

ነዋሪዎቹ አክለውም በከተማችን የተከናወኑ የሰላምና ልማት ተግባራት ውጤታማና ልምድ የሚወሰድባቸው ናቸው ብለዋል።

ከነዋሪዎች መካከል ወይዘሮ ያልጋ ጌታሁን ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት፣ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በከተማው እየተካሄዱ የሚገኙ የልማት ስራዎች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት እያሳደጉ ነው።

በከተማዋ የኮሪደር ልማት፣ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ የአስፋልት መንገድ፣ የሳይንስና የፈጠራ ማዕከል፣ ዲጂታል ቤተ መጽሐፍትና የሥራ እድል መፍጠሪያ ሼዶች እየተገነቡ ይገኛሉ ብለዋል።

እየተገነቡ የሚገኙት የልማት ስራዎችም የከተማውን ውበትና ገጽታ ከማሳመር ባለፈ ኢኮኖሚው እንዲነቃቃ እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።

ይህም ''ወልዲያ ሰላም እንዳልሆነችና በችግር ውስጥ የምንኖር ለሚመስላቸውም አካላት በከፍተኛ የልማት ጉዞ ላይ መሆናችን በተግባር በማሳየት ምላሽ የሰጠ ነው'' ያሉ ሲሆን በዚህም ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ልማቱን በማስቀጠልም ልጆቻችን የስራ እድል እንዲያገኙ፣ ኢኮኖሚው እንዲነቃቃና ከተማችን የቱሪስትና የኢንቨስትመንት መዳረሻ ለማድረግ ከመንግስት ጎን ተሰልፈን እንሰራለን ብለዋል።

ሌላዋ የከተማው ነዋሪ ወይዘሮ ተጓዳ ፍቅሩ በበኩላቸው በሰጡት አስተያየት በሌሎች ከተሞች የተከናወነው የኮሪደርና ሌሎች የልማት ስራዎች አሁን በከተማዋ ተተግብሮ በማየታቸው መደሰታቸውን ገልፀዋል።

ይህም የከተማ አስተዳደሩ ከህብረተሰቡ ጋር በመተባበር ሰላምን ከማስጠበቅ ጎን ለጎን ለልማት ስራዎች ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በመስራቱ የመጣ ውጤት መሆኑን ገልጸዋል።

"እኛም ከመንግስታችን ጎን ተሰልፈን የልማት አርበኛና የሰላም ዘብ በመሆን በዘላቂነት ለመስራት ቆርጠን ተነስተናል" ብለዋል።

አቶ ቸርነት እሸቴ በበኩላቸው የኮሪደር ልማት፣ የመንገድ፣ የወጣቶች መዝናኛ፣ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትና ሌሎችም በፍጥነትና በጥራት ተገንብተው ለአገልግሎት ክፍት መደረጋቸው ከተማዋ በፈጣን ልማትና ዕድገት ላይ ለመሆኗ ማሳያ ናቸው ብለዋል።

በመሆኑም ከተማዋ መማሪያና ልምድ የሚወሰድባት በመሆኗ ተደስተናል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026