የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በክልሉ መንግስታዊ አሰራርን ለማቀላጠፍ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተደራሽነት እየተስፋፋ ነው

Jun 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ቁሊቶ፤ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ተደራሽነት በማስፋት ለመንግስታዊ አሰራር ጥራትና ቅልጥፍና ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ።

ርዕሰ መስተዳድሩ የሀላባ ቁሊቶን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ዛሬ መርቀው ሥራ አስጀምረዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ በክልሉ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ተደራሽነት በማስፋት ለማህበረሰቡ ፈጣንና ጥራት ያለው አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል።


መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተበታተኑ አገልግሎቶችን በማሰባሰብ ማህበረሰቡ አገልግሎት በአንድ ቦታ በቅርበት እንዲያገኝ በማድረግ በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።

በዚህም ማህበረሰቡ የተለያዩ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከቦታ ቦታ ሲንቀሳቀስ የሚገጥመውን እንግልት ከማስቀረት ባለፈ ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኝ ማስቻሉን እንዳሻው (ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡

በቀጣይም በክልሉ አገልግሎትን በማስፋት ለማህበረሰቡ ቀልጣፋና ጥራት ያለው አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሰል የልማት ሥራዎችን አጠናክሮ የማስቀጠል ሥራም በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ አያይዘው ገልጸዋል።

የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙህዲን ሁሴን በበኩላቸው፤ መንግስት ለማህበረሰቡ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ ዘርፈ ብዙ አማራጮችን ተግባራዊ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል።


መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዲጂታል አገልግሎት አሰጣጥን በማቀላጠፍ የማህበረሰቡን እንግልት የሚያስቀር መሆኑንም ጠቁመዋል።

ዛሬ የተመረቀው የሃላባ ቁሊቶ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በሦስት የፌዴራል ተቋማት እና በአራት የክልል ተቋማት 42 አገልግሎቶችን በአንድ ቦታ ለመስጠት እንደሚያስችልም ገልጸዋል።

ማዕከሉ የመንግስት አገልግሎትን ለማግኘት ማህበረሰቡ ከቦታ ቦታ የሚያደርገውን እንቅስቃሴ የሚያስቀር መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ገመዳ መሀመድ ናቸው፡፡


ማዕከሉ ለከተማዋ ነዋሪዎች ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድግ መሆኑን ተናግረዋል።

በአገልግሎቱ ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራሮች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026