🔇Unmute
ቁሊቶ፤ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ተደራሽነት በማስፋት ለመንግስታዊ አሰራር ጥራትና ቅልጥፍና ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ።
ርዕሰ መስተዳድሩ የሀላባ ቁሊቶን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ዛሬ መርቀው ሥራ አስጀምረዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ በክልሉ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ተደራሽነት በማስፋት ለማህበረሰቡ ፈጣንና ጥራት ያለው አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል።

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተበታተኑ አገልግሎቶችን በማሰባሰብ ማህበረሰቡ አገልግሎት በአንድ ቦታ በቅርበት እንዲያገኝ በማድረግ በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።
በዚህም ማህበረሰቡ የተለያዩ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከቦታ ቦታ ሲንቀሳቀስ የሚገጥመውን እንግልት ከማስቀረት ባለፈ ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኝ ማስቻሉን እንዳሻው (ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡
በቀጣይም በክልሉ አገልግሎትን በማስፋት ለማህበረሰቡ ቀልጣፋና ጥራት ያለው አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሰል የልማት ሥራዎችን አጠናክሮ የማስቀጠል ሥራም በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ አያይዘው ገልጸዋል።
የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙህዲን ሁሴን በበኩላቸው፤ መንግስት ለማህበረሰቡ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ ዘርፈ ብዙ አማራጮችን ተግባራዊ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዲጂታል አገልግሎት አሰጣጥን በማቀላጠፍ የማህበረሰቡን እንግልት የሚያስቀር መሆኑንም ጠቁመዋል።
ዛሬ የተመረቀው የሃላባ ቁሊቶ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በሦስት የፌዴራል ተቋማት እና በአራት የክልል ተቋማት 42 አገልግሎቶችን በአንድ ቦታ ለመስጠት እንደሚያስችልም ገልጸዋል።
ማዕከሉ የመንግስት አገልግሎትን ለማግኘት ማህበረሰቡ ከቦታ ቦታ የሚያደርገውን እንቅስቃሴ የሚያስቀር መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ገመዳ መሀመድ ናቸው፡፡

ማዕከሉ ለከተማዋ ነዋሪዎች ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድግ መሆኑን ተናግረዋል።
በአገልግሎቱ ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራሮች ተሳትፈዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026