የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በክልሉ ቡናን በክላስተር በማምረት ጥራቱንና የማሳ ሽፋኑን የማሳደግ ስራ እየተከናወነ ነው- ባለስልጣኑ

Jun 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሃዋሳ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በሲዳማ ክልል ቡናን በክላስተር በማምረት ጥራቱንና የማሳ ሽፋኑን የማሳደግ ስራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ቡና ፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን አስታወቀ፡፡

የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ መስፍን ቃሬ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ ቡናን በክላስተር በማምረት የማሳ ሽፋን እና ጥራቱን የማሳደግ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል፡፡


ለአብነትም በ2015 ዓ.ም በ25 ክላስተሮች የተጀመረው ቡናን የማልማት ስራ አሁን ላይ ወደ 239 ለማሳደግ መቻሉን ገልፀዋል።

በዘንድሮው ዓመትም በእያንዳንዱ ቀበሌ ሁለት ሁለት ክላስተሮችን እንዲኖሩ በማድረግ ቡናን የማልማት ስራን ከፍ የማድረግ እቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የቡና ማሳን ለማስፋት በየአመቱ የችግኝ ተከላ እንደሚካሄድ የገለጹት ዳይሬክተሩ በዘንድሮ ዓመት 36 ነጥብ 5 ሚሊዮን የቡና ችግኝ መተከሉን ገልፀዋል።

በአሁኑ ወቅት የቡና ምርታማነት ማሻሻያ ፓኬጆችን ተግባራዊ በማድረግ በአለም አቀፍ ገበያ ተወዳሪ ለመሆን እየተሰራ መሆኑንም ገልፀዋል።

በዘንድሮ ዓመት 31 ሺህ ሔክታር መሬት ላይ የሚገኙ ያረጁ ቡናዎች የማደስ ስራ መሰራቱንም ነው ያነሱት።

በተለይም በክልሉ የሚመረተው ቡና ተፈጥሯዊ ጣእሙን የጠበቀ እንዲሆን የተፈጥሮ ማዳበሪያ አዘገጃጀትና አጠቃቀም ላይ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

በዚህም ባለፉት ሁለት ዓመታት ከቡና ኢንዱስትሪዎች የሚወጣውን የቡና ገለፈት ወደ ተፈጥሮ ማዳበሪያነት የመቀየር ስራም እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ይህም ያጋጥም የነበረውን የአካባቢ ብክለት ከማስቀረት ባሻገር የቡና ጥራትና ምርታማነት በማረጋገጥ ረገድ ጉልህ ሚና የሚያበረክት እንደሆነም ገልፀዋል፡፡

በክልሉ ያሉ 220 የቡና ማዘጋጃ ኢንዱስትሪዎቹ መደበኛና ቨርሚ ኮምፖስት አዘጋጅተው ለአርሶ አደሩ እንዲያቀርቡ መደረጉንም ነው የተናገሩት፡፡

በማእከላዊ ሲዳማ ዞን የዳሌ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ባልቻ በላይነህ በበኩላቸው፤ በወረዳው ከሚገኙ 32 ቀበሌዎች ውስጥ ሃያ አንዱ ሙሉ በሙሉ ቡና አምራች መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

ለዚህም በወረዳው የቡና ማዘጋጃ ኢንዱስትሪዎችና በተደራጁ ወጣቶች የቡና ጥራት፣ምርታማነትና ተፈጥሮአዊ ጣእም የሚያስጠብቁ የተፈጥሮ ማዳበሪያ (ኮምፓስት) እያዘጋጁ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ይሕም ያጋጥም የነበረውን የአካባቢ ብክለት ከመከላከል ባለፈ ቡና ከአርሶ አደሩ ጋር ትስስር ለመፍጠር እና ጥራትን ለማስጠበቅ እያስቻለ መሆኑን ጠቅሰዋል።


በዳሌ ወረዳ የሾኤ ቀበሌው ሞዴል አርሶ አደር አሰፋ ደበቆ በ 3 ነጥብ 5 ሄክታር ማሳ ላይ ቡና እያለሙ መሆኑን ነው የሚናገሩት ፡፡

የቡና ጥራትና ምርታማነት ለማረጋገጥ ከችግኝ መረጣ እስከ ምርት አሰባሰብ ድረስ በባለሙያ የታገዘ እንክብካቤ እንደሚያደርጉ ገልጸው የተፈጥሮ ማዳበሪያ፣ጥላ ዛፍና ደባል ሰብሎችን እንደከተሉ ገልጸዋል፡፡


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026