የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በነቀምቴ ከተማ ህብረተሰቡ ለሰላምና ልማት መጠናከር ባሳየው ቁርጠኝነት ስኬታማ ሥራዎች ተከናውነዋል

Jun 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ነቀምቴ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በነቀምቴ ከተማ ህብረተሰቡ ለሰላምና ልማት መጠናከር ባሳየው ቁርጠኝነት በርካታ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የኦሮሚያ ክልል ፀጥታ እና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ኮሚሽነር አራርሳ መርዳሳ ገለጹ።

በነቀምቴ ከተማ በ189 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነቡ ሼዶች ዛሬ ተመርቀዋል።


በሼዶቹ ምረቃ ላይ የኦሮሚያ ክልል ፀጥታ እና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ኮሚሽነር አራርሳ መርዳሳ፣ የክልሉ ሲቪል ሰርቪስና የሰው ሀብት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ኮከቤ ዲዳ፣ የነቀምቴ ከተማ ከንቲባ መሰረት ሀይሉ እና ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

ኮሚሽነር አራርሳ መርዳሳ የከተማውንና አካባቢውን ሰላም ለማጠናከር ህብረተሰቡን ከፀጥታ አካላት ጋር በማስተባበር በተሰራው ሥራ የአካባቢው ሰላም ማጠናከርና የልማት ሥራዎችን በስፋት ማከናወን መቻሉን ተናግረዋል።

በተለይ ለከተማው ወጣቶች የሥራ አማራጭ እየተመቻቸ መሆኑን ጠቅሰው፤ ወጣቶችም የሥራ ዕድሉን በአግባቡ በመጠቀም ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች መትረፍ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

የነቀምቴ ከተማ ከንቲባ መሰረት ሀይሉ በበኩላቸው በከተማዋ ሰፊ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልፀዋል።


ማህበረሰቡ ለሰላሙ ዘብ ቆሞ ለልማት ባሳየው ቁርጠኝነት የተጀመሩ የልማት ሥራዎች በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ተጠናቀው ለአገልግሎት እየበቁ መሆኑን ተናግረዋል።

ዛሬ ተመርቀው ለአገልግሎት በበቁት ሼዶችም ወጣቶች ሰርተው ራሳቸውን እንዲለውጡ ለማስቻል የከተማዋ አስተዳደሩ የቅርብ ክትትልና ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።

የነቀምቴ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤት ኃላፊ አቶ ቶለሳ ደጋጎ ዛሬ ለምረቃ የበቁት ሼዶች በመንግሥት 189 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገባቸው መሆኑን ተናግረዋል።


ሼዶቹም በ104 ማህበራት ለተደራጁ 520 ወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር የሚያስችሉ መሆኑን ገልጸው፤ ወጣቶቹም በከብት ማድለብ፣ በሥጋና እንቁላል ዶሮ እርባታ፣ በወተት ልማትና በመሰል የሥራ ዘርፎች የተደራጁ ናቸው ብለዋል።

የሥራ ዕድል ከተፈጠረላቸው ወጣቶች መካከል ወጣት ሙሉጌታ መልካሙ ከጓደኞቹ ጋር በወተት ምርት በመደራጀት በአምስት ሚሊየን ብር ካፒታል ሥራ ለመጀመር መዘጋጀታቸውንም ተናግሯል።


የከተማ አስተዳደሩ ያመቻቸላቸውን እድል በመጠቀም ሰርተው ራሳቸውን ለመለወጥ ማቀዳቸውን ተናግሯል።

ሌላኛው የሥራ እድል ተጠቃሚ ወጣት ቢቂላ ለማ በበኩሉ ከብት በማድለብ ሥራ ላይ ለመሰማራት እንደተደራጁ ገልጾ፤ በስራቸው ውጤታማ ለመሆን ተግተው እንደሚሰሩ አመልክቷል።

መንግስት ያመቻቸውን የሥራ እድል በመጠቀም ሰርቶ ለመለወጥ ቁርጠኛ መሆኑንም አረጋግጧል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026