የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ኢትዮጵያ ያላትን የማዕድን ሀብት ወደ ተጨባጭ ብሔራዊ ዕድገት አቅም እየቀየረች ነው- ኢንጂነር ሐና ብርሃኑ

Jun 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ያላትን የማዕድን ሀብት ወደ ተጨባጭ ብሔራዊ ዕድገት አቅም እየቀየረች መሆኑን የማዕድን ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሐና ብርሃኑ ገለጹ።


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት፣ “ከለውጥ ወደ ዘላቂ ሽግግር” በሚል መሪ ሀሳብ የ“ኢትዮጵያ ታከናውናለች” ሀገራዊ ጉባኤ በሳይንስ ሙዚየም ተካሂዷል።


የማዕድን ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሐና ብርሃኑ በመድረኩ የዘርፉን የትራንስፎርሜሽን ጉዞ አስመልክቶ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል።


ኢንጂነር ሐና በማብራሪያቸው፤ ኢትዮጵያ ያላትን ሰፊ የማዕድን ሀብት በተቀናጀ መልክ ወደ ተጨባጭ ብሔራዊ የኢኮኖሚ ዕድገት አቅም እየቀየረች መሆኑን ገልጸዋል።


የሀገሪቱ የማዕድን ዘርፍ ቀደም ሲል ከነበረበት ደካማ አፈጻጸምና ተግዳሮቶች ተነስቶ፣ በአሁኑ ወቅት ከኢኮኖሚ ዕድገት ስትራቴጂካዊ ምሰሶዎች አንዱ መሆን መቻሉንም አብራርተዋል።


ይህ ዓይነቱ ስር ነቀል ለውጥ ሊመዘገብ የቻለው መንግሥት በወሰዳቸው ቁርጠኛ የፖሊሲ ማሻሻያዎች፣ የገበያ ሥርዓቱን በማስተካከል እና እሴትን መጨመር በሚያስችሉ መጠነ-ሰፊ ኢንቨስትመንቶች በመታገዙ መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታዋ አስገንዝበዋል።


ሪፎርሙን ተከትሎ ማዕድንና ነዳጅን እንደ እምቅ አቅም ብቻ ከማውራት ባለፈ፣ተጨባጭ ውጤት ወደሚያስመዘግብ ስትራቴጂካዊ አቅም እንዲሸጋገር መደረጉን አመልክተዋል።


መንግሥት በዘርፉ የነበሩ የአሠራር እንቅፋቶችን ለማስወገድ ህግጋትን ያሻሻለ ሲሆን፣ ግልጽነትን ለማረጋገጥም የዲጂታል አሠራሮችን ማስተዋወቁን አመልክተዋል።


አሁን የተዘረጋው ሥርዓት ዘርፉን ከቁጥጥር ባለፈ ከኢንቨስተሮች ጋር ጠንካራ አጋርነት በመፍጠር ለአስተማማኝና ለረጅም ጊዜ ኢንቨስትመንት ምቹ እንዲሆን አድርጎታል ብለዋል።


በአሁኑ ወቅት ዘርፉ ከፍተኛ የወጪ ንግድ ኤክስፖርት ገቢን ለሀገር እያስገኘ ሲሆን፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን ጥገኝነት በከፍተኛ ሁኔታ በመቀነስ ረገድ ከፍተኛ ስኬቶች ተመዝግበዋል ብለዋል፡፡


ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ለከሰል ድንጋይ ማስገቢያ በየዓመቱ ከ300 ሚሊዮን ዶላር በላይ ታወጣ የነበረ ቢሆንም፣ በአሁኑ ወቅት የሀገር ውስጥ አምራቾችንና የግል ባለሀብቶችን በማበረታታት የሀገሪቱን ፍላጎት ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ምርት መሸፈን መቻሉን ገልጸዋል።


የሲሚንቶ ምርትን ለማሳደግ በተደረገው ጥረት ባለፉት ስምንት ዓመታት ውስጥ የሀገሪቱ ዓመታዊ የሲሚንቶ ምርት ከ8 ሚሊዮን ቶን ወደ 14 ሚሊዮን ቶን በማደጉ ገበያውን ማረጋጋት መቻሉን አስታውቀዋል።


በወርቅ፣በስትራቴጂካዊና ወሳኝ ማዕድናት፣በነዳጅ እንዲሁም በማዳበሪያ ምርት ላይ እየተስፋፉ የመጡት አዳዲስ ኢንቨስትመንቶች የለውጡ ማሳያ መሆናቸውን ገልጸዋል።


በማዕድኑ ዘርፍ እየታዩ ያሉ ስኬቶች የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ፣የስትራቴጂካዊ ርዕይ እና የተቀናጀ የአፈጻጸም ድምር ውጤት መሆናቸውን ኢንጂነር ሐና ገልጸዋል።


በአሁኑ ወቅትም የማዕድንና ነዳጅ ዘርፍ የሀገሪቱን ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ ዕድገት ወደ ላቀ ደረጃ እንዲያሸጋግር በትኩረት እየተሠራበት መሆኑ አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026