የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በክልሉ የቱሪዝም ዘርፉን ይበልጥ ለማጎልበት የሚያስችሉ የልማት ስራዎች በስፋት እየተተገበሩ ይገኛሉ 

Jun 25, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሐረር ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የቱሪዝም ዘርፉን ይበልጥ ለማሳደግና ለማጎልበት የሚያስችሉ የኢንቨስትመንትና የልማት ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ተናገሩ።

ርዕሰ መስተዳድሩ ኦርዲን በድሪ በሐረር ከተማ በግንባታ ላይ ያሉ የተለያዩ ኢንቨስትመንቶችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

የሐረሪ ክልል በተለይም ጥንታዊቷ የጀጎል ግንብ የዓለም ቅርስነት ከተመዘገበበት ጊዜ ጀምሮ በኢትዮጵያ ቀዳሚ ከሆኑ የባህልና የታሪክ ቱሪዝም መዳረሻዎች አንዷ ናት።

ከተማዋ ያላት ልዩ የእስልምና ታሪክ ቅርሶች፣ የሀረሪ ባህላዊ ቤቶች፣ የጅብ መመገብ ልማድ እንዲሁም የህዝቡ የአብሮነትና የሙዚቃ ባህል በየዓመቱ በርካታ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ጎብኝዎችን ይስባል።


የክልሉ መንግስትም በቅርብ ዓመታት ውስጥ በርካታ የሪፎርም እና የልማት ስራዎችን በማከናወን ላይ ሲሆን፥ በተለይም የቱሪዝም ዘርፉን በግል ባለሀብቱ ኢንቨስትመንት እገዛ ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንዳሉት የክልሉ መንግስት በኢንቨስትመንት አማራጮች ላይ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች አስፈላጊውን ማበረታቻና ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠሩን አንስተዋል።

በክልሉ ለኢንቨስትመንት ዘርፍ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር በተደረገው የተቀናጀ ጥረትም አመርቂ ለውጥ መመዝገቡን ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት በከተማው በግል ባለሀብቶች እየተገነቡ ያሉ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችም አበረታች ደረጃ ላይ እንደሚገኙ ገልጸው፤ የግንባታ ስራዎቹም በታቀደላቸው የጊዜ ሰሌዳ እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰዋል።

የልማት ፕሮጀክቶቹ የክልሉን የቱሪዝም አቅም ለማሳደግና ለዜጎች የሚሆን የሥራ ዕድልን በስፋት ለመፍጠር ያላቸው ፋይዳም ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመዋል።


በኢንቨስትመንት አማራጮች ላይ ተሰማርተው አበረታች አፈጻጸም እያሳዩ ላሉ ባለሀብቶች፣ የክልሉ መንግስት የሚያደርገውን ዘርፈ ብዙ ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ርዕሰ መስተዳድሩ አረጋግጠዋል።

ባለሀብቶቹም የጀመሩትን የግንባታ ስራ በፍጥነትና በጥራት አጠናቀው ለአገልግሎት ማብቃት እንዳለባቸውም ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ ባካሄዱት በዚህ ምልከታ ላይ የክልሉ ኢንቨስትመንት ቦርድ አባላትን ጨምሮ ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች መታደማቸው ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026