የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በክልሉ የቱሪዝም ዘርፉን ይበልጥ ለማጎልበት የሚያስችሉ የልማት ስራዎች በስፋት እየተተገበሩ ይገኛሉ 

Jun 25, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሐረር ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የቱሪዝም ዘርፉን ይበልጥ ለማሳደግና ለማጎልበት የሚያስችሉ የኢንቨስትመንትና የልማት ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ተናገሩ።

ርዕሰ መስተዳድሩ ኦርዲን በድሪ በሐረር ከተማ በግንባታ ላይ ያሉ የተለያዩ ኢንቨስትመንቶችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

የሐረሪ ክልል በተለይም ጥንታዊቷ የጀጎል ግንብ የዓለም ቅርስነት ከተመዘገበበት ጊዜ ጀምሮ በኢትዮጵያ ቀዳሚ ከሆኑ የባህልና የታሪክ ቱሪዝም መዳረሻዎች አንዷ ናት።

ከተማዋ ያላት ልዩ የእስልምና ታሪክ ቅርሶች፣ የሀረሪ ባህላዊ ቤቶች፣ የጅብ መመገብ ልማድ እንዲሁም የህዝቡ የአብሮነትና የሙዚቃ ባህል በየዓመቱ በርካታ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ጎብኝዎችን ይስባል።


የክልሉ መንግስትም በቅርብ ዓመታት ውስጥ በርካታ የሪፎርም እና የልማት ስራዎችን በማከናወን ላይ ሲሆን፥ በተለይም የቱሪዝም ዘርፉን በግል ባለሀብቱ ኢንቨስትመንት እገዛ ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንዳሉት የክልሉ መንግስት በኢንቨስትመንት አማራጮች ላይ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች አስፈላጊውን ማበረታቻና ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠሩን አንስተዋል።

በክልሉ ለኢንቨስትመንት ዘርፍ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር በተደረገው የተቀናጀ ጥረትም አመርቂ ለውጥ መመዝገቡን ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት በከተማው በግል ባለሀብቶች እየተገነቡ ያሉ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችም አበረታች ደረጃ ላይ እንደሚገኙ ገልጸው፤ የግንባታ ስራዎቹም በታቀደላቸው የጊዜ ሰሌዳ እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰዋል።

የልማት ፕሮጀክቶቹ የክልሉን የቱሪዝም አቅም ለማሳደግና ለዜጎች የሚሆን የሥራ ዕድልን በስፋት ለመፍጠር ያላቸው ፋይዳም ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመዋል።


በኢንቨስትመንት አማራጮች ላይ ተሰማርተው አበረታች አፈጻጸም እያሳዩ ላሉ ባለሀብቶች፣ የክልሉ መንግስት የሚያደርገውን ዘርፈ ብዙ ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ርዕሰ መስተዳድሩ አረጋግጠዋል።

ባለሀብቶቹም የጀመሩትን የግንባታ ስራ በፍጥነትና በጥራት አጠናቀው ለአገልግሎት ማብቃት እንዳለባቸውም ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ ባካሄዱት በዚህ ምልከታ ላይ የክልሉ ኢንቨስትመንት ቦርድ አባላትን ጨምሮ ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች መታደማቸው ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026