የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በዞኑ የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች በስፋት እየተከናወኑ ነው

Jun 25, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጊምቢ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በምዕራብ ወለጋ ዞን የህዝቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች በስፋት እየተከናወኑ መሆናቸውን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።

በምዕራብ ወለጋ ዞን ቆንዳላ ወረዳ ግንባታቸው የተጠናቀቁ የተለያዩ መሰረተ ልማት ግንባታዎች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል።


በወቅቱም የኦሮሚያ ክልል የመንገድ እና ሎጂስቲክስ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ታዬ ጉዲሳ በክልሉ ህዝቡን ተጠቃሚ ያደረጉ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች እየተከናወኑ ናቸው።

መሰረተ ልማቱም በአጭር እና በረጅም ጊዜ እቅድ የተገነቡ መሆኑንና በህዝቡና በአጋር አካላት ተሳትፎ መከናወናቸውን ጠቅሰው ተግባራቱም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።


የክልሉ መንግስት የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ ባለው ቁርጠኝነት በርካታ የልማት ስራዎች መከናወናቸውን ያነሱት ኃላፊው ዛሬ በዞኑ የተመረቁት ፕሮጀክቶችም የዚሁ ማሳያ መሆናቸውን ተናግረዋል።


የምዕራብ ወለጋ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ተሊላ ተረፈ በበኩላቸው በዞኑ ለነዋሪዎች የመሰረተ ልማት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ግንባታዎች በጥራትና በተያዘላቸው ጊዜ ተገንብተው ለአገልግሎት እንዲበቁ እየተሰራ ነው ብለዋል።


የዚሁ አካል የሆኑትና በበጀት ዓመቱ ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡ የተለያዩ መሠረተ ልማቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት መብቃታቸውን ተናግረዋል።

በቀጣይም በዞኑ የህዝቡን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026