🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 20/2018 (ኢዜአ)፦ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ተመራቂዎች የኢትዮጵያን የዲጂታል ጉዞ ለማፋጠን ዕውቀታቸውን ወደ ፈጠራ ማሸጋገር እንዳለባቸው የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተርና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ቦርድ ሰብሳቢ ትዕግሥት ሀሚድ ገለጹ።
የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በቅድመ ምረቃ፣ በድህረ ምረቃ እና በሦስተኛ ዲግሪ በመደበኛና በተከታታይ የትምህርት ፕሮግራሞች ያሰለጠናቸውን 1 ሺህ 246 ተማሪዎች አስመርቋል።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተርና የዩኒቨርሲቲው የቦርድ ሰብሳቢ ትዕግሥት ሀሚድ ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የኢትዮጵያን የዲጂታል ጉዞ ዳር ለማድረስ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ባለሙያዎችን ማፍራት ያስፈልጋል ብለዋል።
ሀገሪቱ አሁን ካለችበት የኢኮኖሚና የቴክኖሎጂ ደረጃ ከፍ እንድትል የሳይንስና ቴክኖሎጂ ተመራቂዎች ሚና ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።
የዛሬ ተመራቂ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ያገኙትን ዕውቀት ወደ ፈጠራና ወደ ኢንዱስትሪ ምርታማነት አቅም እንዲቀይሩ በማስገንዘብ ሀገራቸውን በቅንነት እንዲያገለግሉ ጥሪ አቅርበዋል።
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ በበኩላቸው፤ ባለፉት ዓመታት በሀገር አቀፍ ደረጃ የትምህርት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ሰፊ ሥራ መሠራቱን ተናግረዋል።
ትምህርት ግቡን እንዲመታ ከተደራሽነቱ ባሻገር ጥራቱን ማረጋገጥ የግድ መሆኑን ጠቅሰው፥ መንግሥት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ብቁና ተመራማሪ ትውልድ ለማፍራት የአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማረጋገጫ ሪፎርም አድርጎ ወደ ሥራ መግባቱን አብራርተዋል።
በዚህም ሳይንስና ቴክኖሎጂን ጨምሮ የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ ረገድ ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገባቸውን ነው የገለጹት።
የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ደረጄ እንግዳ (ዶ/ር)፤ ዩኒቨርሲቲው ተማሪዎችን ሲያስመርቅ የዘንድሮው ለ12ኛ ጊዜ መሆኑን ገልጸዋል።
ዩኒቨርሲቲው የኢትዮጵያን የልማት ግቦች ለማሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝም ገልጸዋል።
ተመራቂ ተማሪዎች በተግባር ተኮር የቴክኖሎጂ ፈጠራና በኢንዱስትሪዎች ውስጥ በሚታዩ ተጨባጭ ችግሮች ላይ ያተኮሩ ችግር ፈች የምርምር ሥራዎችን ማከናወናቸውን አመላክተዋል።
ዩኒቨርሲቲው የቴክኖሎጂ ሽግግርን በማሳለጥ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነቱን በእጅጉ እያሳደገ እንደሚገኝ አንስተዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026