የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የኢጋድ የሳይበር የተግባር ልምምድ የአባል ሀገራትን የጋራ ደህንነት ለማረጋገጥና ተሞክሮ ለመለዋወጥ ትልቅ ዕድል ፈጥሯል

Jul 1, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ የኢጋድ የሳይበር የተግባር ልምምድ የአባል ሀገራትን የጋራ ደህንነት ለማረጋገጥና ተሞክሮ ለመለዋወጥ ትልቅ ዕድል እንደፈጠረላቸው አስተያየታቸውን የሰጡ የስልጠናው ተሳታፊ ሀገራት ተወካዮች ገለጹ።

የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢንሣ) ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የኢጋድ ቀጣናዊ የሳይበር የተግባር ልምምድ ሥልጠና ላለፋት አምስት ቀናት በአዲስ አበባ ተሰጥቷል።


በመርሃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያን ጨምሮ ዩጋንዳ፣ ኬንያ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሶማሊያ እና የጅቡቲ ተወካዮች ተሳትፈዋል።

በጅቡቲ የሚገኘው የኢጋድ ዋና መሥሪያ ቤት የሳይበር ደህንነት እና የዳታ አስተዳደር ከፍተኛ ባለሙያ ኸድራ አሊ ዩሱፍ እንደገለጹት፤ ሥልጠናው ከፖሊሲ ቀረጻ ጀምሮ እስከ ቴክኒካዊ ልምምድ ድረስ ያሉ በርካታ ዘርፎችን ያካተተ ነበር ብለዋል።

በተለይም የሳይበር ደህንነት ሥጋት መረጃ ትንተና እና የማልዌር ወይም የጎጂ ሶፍትዌሮች ምርመራ ላይ ሰፊ ትኩረት መደረጉን አመልክተዋል።

የሳይበር ሥጋቶችና ጥቃቶች በተፈጥሮ ድንበር ተሻጋሪ በመሆናቸው መርሃ ግብሩ በአባል አገራቱ መካከል ያለውን የጋራ የመከላከል አቅም እና ቀጣናዊ ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል።


በኡጋንዳ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ውስጥ ዋና የሲስተምስ አድሚኒስትሬተር ሮበርት ልዋሳ እንደተናገሩት፤ መርሃ ግብሩ እንደ ኢትዮጵያና ዩጋንዳ ያሉ የኢጋድ አባል አገራት የሳይበር ደኅንነትን እንዴት እየተገበሩት እንደሆነና ያላቸውን የአስተዳደር መዋቅር እርስ በእርስ ለመለዋወጥ ትልቅ ዕድል የፈጠረ ነው ብለዋል።

የሳይበር ጥቃት ድንበር ተሻጋሪና ዓለም አቀፋዊ ሥጋት መሆኑን በመጥቀስ ጥቃቶቹን ለመቋቋም ቀጣይነት ያለው የአቅም ግንባታና አብሮ መስራት ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል።


በደቡብ ሱዳን የብሔራዊ የሳይበር ደህንነት ቁጥጥር ማዕከል አናሊስት ዮም ማሉአል ማጆክ በበኩላቸው፤ ሥልጠናው ሙሉ በሙሉ በተግባር እና በእውነተኛው ዓለም ላይ ሊያጋጥሙ የሚችሉ የሳይበር ጥቃቶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

በመሆኑም በየአገራቱ የሚገኙ የመንግሥት መሠረተ ልማቶችን፣ የፋይናንስ ሥርዓቶችን እና የግል ተቋማትን ከጥቃት ለመጠበቅ የትኞቹ ሰርቨሮችና ሥርዓቶች ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባ ትልቅ ግንዛቤ ያገኘንበት ነው ብላለች።

ወደ አገራቸው ሲመለሱም ይህንን ተግባራዊ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል።


የሶማሊያ ኮሙኒኬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የኮምፒውተርና መረጃ ቴክኖሎጂ ዳይሬክተር ሀሰን ሁሴን መሐመድ በበኩላቸው ሥልጠናው እጅግ አስደናቂና ከፍተኛ እውቀት የተገኘበት መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይም ኢትዮጵያ በሳይበር ደኅንነት ዘርፍ ያላትን ልምድና ያሳየችውን ዕድገት ማጋራቷ ለአባል አገራቱ ጠቃሚ መሆኑን ጠቁመዋል።

ከተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ከመጡ ከፍተኛ ባለሙያዎችም ሰፊ እውቀትና ልምድ ማግኘታቸውን በመግለጽ ተሳታፊዎቹ በሥልጠናው መደሰታቸውን አክለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026