የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ኢትዮጵያ የብዝሃ ኢኮኖሚ ዘርፍ አቅጣጫን ተግባራዊ በማድረጓ በሁሉም መስክ ፈጣንና ተከታታይነት ያለው ዕድገት ማስመዝገብ ችላለች - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

Jul 1, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ የብዝሃ ኢኮኖሚ ዘርፍ አቅጣጫን ተግባራዊ በማድረጓ በሁሉም መስክ ፈጣንና ተከታታይነት ያለው ዕድገት ማስመዝገብ መቻሏን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

ኢትዮጵያ ከለውጡ ወዲህ ከግብርና መር የኢኮኖሚ አቅጣጫ ወደ ብዝሃ ዘርፍ የኢኮኖሚ አቅጣጫ መሸጋገሯ ይታወሳል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ ብዝሃ ዘርፍ የኢኮኖሚ አቅጣጫ መከተል ከጀመረች ወዲህ በሁሉም ዘርፎች የሚያስደንቅ ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል፡፡

በግብርና ዘርፍ በስንዴ፣ በቡና፣ በሩዝ፣ በፍራፍሬ፣ በሌማት ትሩፋት፣ በዶሮና ወተት የተገኙ ውጤቶች አስደናቂ ናቸው ብለዋል፡፡

በቴክኖሎጂ ዘርፍም በ5 ሚሊዮን ኮደርስ፣ በዲጂታል መታወቂያ፣ በሞባይል መኒ፣ በቴሌ ብር አንጸባራቂ ውጤቶች መመዝገባቸውን አንስተዋል፡፡

የኢንዱስትሪ ዘርፍም ለዘመናት ውስን አቅም የነበረው ዘርፍ እንደነበር አውስተው፤ አሁን ላይ ግን እጅግ በተሻለ ሁኔታ እያደገ እንደሚገኝ አንስተዋል፡፡

ከዘርፉ የሚገኙ ምርቶችን ወደ ውጭ በመላክ የውጭ ምንዛሬ ምንጭ ሆኖ እያገለገለ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡

ከ30 እስከ 40 ሚሊዮን ዶላር ማስገባት ሳይችል የቆየው የማዕድን ዘርፍ አሁን ላይ ቢሊዮን ዶላር የሚገኝበት ዘርፍ መሆኑን አመላክተዋል፡፡

በዚህ ዓመት ከአጠቃላይ ወጪ ንግድ ከ10 ነጥብ 78 እስከ 11 ቢሊዮን ዶላር ገቢ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡

የብዝሃ ኢኮኖሚ ዘርፍ ተግባራዊ በመደረጉ ሁሉም ዘርፍ የራሱን ድርሻ እንዲያዋጣ እና ኢኮኖሚው በከፍተኛ ደረጃ እንዲያድግ አድርጓል ነው ያሉት።

በመሆኑም በዚህ ዓመት 10 ነጥብ 2 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት እንጠብቃለን ብለዋል፡፡

ዓመታዊ ገቢ የመሰብሰብ አቅም እጅግ በሚያስደንቅ ሁኔታ እያደገ መምጣቱን ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያ በዚህ ዓመት 1 ነጥብ 5 ትሪሊዮን ብር እንደምትሰበስብ ይጠበቃል ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ የብዝሃ ኢኮኖሚ ዘርፍ አቅጣጫን ተግባራዊ በማድረጓ በሁሉም መስክ ፈጣንና ተከታታይነት ያለው ዕድገት ማስመዝገብ መቻሏን ነው የተናገሩት፡፡

ይህም የመንግስትን ትክክለኛ እና የተሳሰረ የፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ያረጋገጠ ነው ብለዋል፡፡


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026