🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት የተከናወኑ ዘርፈ ብዙ ስኬታማ ሥራዎች የታቀዱ ግቦችን ከማሳካት ባለፈ፣ ለዘርፉ ዕድገት ትልቅ አቅም የፈጠሩ መሆናቸውን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማቱ ጋር በመሆን የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸምን እየገመገመ ይገኛል።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር)፤ በበጀት ዓመቱ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱና በተጠሪ ተቋማቱ የተመዘገበው የዕቅድ አፈጻጸም እጅግ ከፍተኛና ስኬታማ እንደነበር አብራርተዋል።
በርካታ ሀገራዊ ሥራዎችም በዓመቱ ለማሳካት ከታቀደው በላይ የላቀ ስኬት እንደተመዘገበባቸው ጠቁመዋል።

ተቋማዊ ሪፎርም በስኬት መከናወኑን ጠቅሰው ለሠራተኞች ምቹ የሆነ የሥራ ከባቢ ከመፍጠር በኩልም አበረታች ተግባራት መከናወናቸውን ጠቁመዋል፡፡
በተለይም የተቋሙን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል የተከናወኑ የአቅም ግንባታ ሥራዎች ውጤታማ መሆናቸውን አንስተው፤ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እና ተጠሪ ተቋማቱ የሚሰጧቸውን አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል ሥርዓት ማሸጋገር መቻሉን ጠቅሰዋል፡፡
በዚህም መሠረት ከንግድ ፈቃድ፣ ምዝገባ፣ ማሻሻያ እና ማደስ ጋር የተያያዙ ከ3 ነጥብ 4 ሚሊየን በላይ አገልግሎቶችን በኦንላይን መስጠት ተችሏል ብለዋል።
የንግድ ሥርዓቱን ማዘመንና የወጪ ንግድን ማሳደግን በተመለከተም ዘርፈ ብዙ ሥራዎች መከናወናቸውን ያነሱት ሚኒስትሩ፤ እነዚህ ስኬቶች ሀገሪቱ በበጀት ዓመቱ ከወጪ ንግድ ለማግኘት ያቀደችውን የ10 ነጥብ 7 ቢሊየን ዶላር ገቢ ግብ ለማሳካት የሚያስችሉና ትልቅ አቅም የፈጠሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በተጨማሪም ዘመናዊ የግብይት ማዕከላትን በማስፋፋት በኩል አበረታች ሥራዎች መከናወናቸውንና በአሁኑ ወቅት የማዕከላቱ ቁጥር ከ31 በላይ መድረሱን ተናግረዋል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞም የ10 ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት የግብይት ማዕከላት ግንባታ የተጀመረ ሲሆን፣ ሁለቱ ተጠናቀው በበጀት ዓመቱ ለአገልግሎት ክፍት መደረጋቸውን አስታውቀዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026