የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በበጀት ዓመቱ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱና ተጠሪ ተቋማት የተከናወኑ ስኬታማ ሥራዎች ለዘርፉ ዕድገት ትልቅ አቅም የፈጠሩ ናቸው

Jul 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት የተከናወኑ ዘርፈ ብዙ ስኬታማ ሥራዎች የታቀዱ ግቦችን ከማሳካት ባለፈ፣ ለዘርፉ ዕድገት ትልቅ አቅም የፈጠሩ መሆናቸውን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ።

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማቱ ጋር በመሆን የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸምን እየገመገመ ይገኛል።

በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር)፤ በበጀት ዓመቱ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱና በተጠሪ ተቋማቱ የተመዘገበው የዕቅድ አፈጻጸም እጅግ ከፍተኛና ስኬታማ እንደነበር አብራርተዋል።

በርካታ ሀገራዊ ሥራዎችም በዓመቱ ለማሳካት ከታቀደው በላይ የላቀ ስኬት እንደተመዘገበባቸው ጠቁመዋል።


ተቋማዊ ሪፎርም በስኬት መከናወኑን ጠቅሰው ለሠራተኞች ምቹ የሆነ የሥራ ከባቢ ከመፍጠር በኩልም አበረታች ተግባራት መከናወናቸውን ጠቁመዋል፡፡

በተለይም የተቋሙን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል የተከናወኑ የአቅም ግንባታ ሥራዎች ውጤታማ መሆናቸውን አንስተው፤ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እና ተጠሪ ተቋማቱ የሚሰጧቸውን አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል ሥርዓት ማሸጋገር መቻሉን ጠቅሰዋል፡፡

በዚህም መሠረት ከንግድ ፈቃድ፣ ምዝገባ፣ ማሻሻያ እና ማደስ ጋር የተያያዙ ከ3 ነጥብ 4 ሚሊየን በላይ አገልግሎቶችን በኦንላይን መስጠት ተችሏል ብለዋል።

የንግድ ሥርዓቱን ማዘመንና የወጪ ንግድን ማሳደግን በተመለከተም ዘርፈ ብዙ ሥራዎች መከናወናቸውን ያነሱት ሚኒስትሩ፤ እነዚህ ስኬቶች ሀገሪቱ በበጀት ዓመቱ ከወጪ ንግድ ለማግኘት ያቀደችውን የ10 ነጥብ 7 ቢሊየን ዶላር ገቢ ግብ ለማሳካት የሚያስችሉና ትልቅ አቅም የፈጠሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በተጨማሪም ዘመናዊ የግብይት ማዕከላትን በማስፋፋት በኩል አበረታች ሥራዎች መከናወናቸውንና በአሁኑ ወቅት የማዕከላቱ ቁጥር ከ31 በላይ መድረሱን ተናግረዋል።

ከዚሁ ጋር ተያይዞም የ10 ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት የግብይት ማዕከላት ግንባታ የተጀመረ ሲሆን፣ ሁለቱ ተጠናቀው በበጀት ዓመቱ ለአገልግሎት ክፍት መደረጋቸውን አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026