የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በበጀት ዓመቱ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱና ተጠሪ ተቋማት የተከናወኑ ስኬታማ ሥራዎች ለዘርፉ ዕድገት ትልቅ አቅም የፈጠሩ ናቸው

Jul 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት የተከናወኑ ዘርፈ ብዙ ስኬታማ ሥራዎች የታቀዱ ግቦችን ከማሳካት ባለፈ፣ ለዘርፉ ዕድገት ትልቅ አቅም የፈጠሩ መሆናቸውን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ።

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማቱ ጋር በመሆን የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸምን እየገመገመ ይገኛል።

በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር)፤ በበጀት ዓመቱ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱና በተጠሪ ተቋማቱ የተመዘገበው የዕቅድ አፈጻጸም እጅግ ከፍተኛና ስኬታማ እንደነበር አብራርተዋል።

በርካታ ሀገራዊ ሥራዎችም በዓመቱ ለማሳካት ከታቀደው በላይ የላቀ ስኬት እንደተመዘገበባቸው ጠቁመዋል።


ተቋማዊ ሪፎርም በስኬት መከናወኑን ጠቅሰው ለሠራተኞች ምቹ የሆነ የሥራ ከባቢ ከመፍጠር በኩልም አበረታች ተግባራት መከናወናቸውን ጠቁመዋል፡፡

በተለይም የተቋሙን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል የተከናወኑ የአቅም ግንባታ ሥራዎች ውጤታማ መሆናቸውን አንስተው፤ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እና ተጠሪ ተቋማቱ የሚሰጧቸውን አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል ሥርዓት ማሸጋገር መቻሉን ጠቅሰዋል፡፡

በዚህም መሠረት ከንግድ ፈቃድ፣ ምዝገባ፣ ማሻሻያ እና ማደስ ጋር የተያያዙ ከ3 ነጥብ 4 ሚሊየን በላይ አገልግሎቶችን በኦንላይን መስጠት ተችሏል ብለዋል።

የንግድ ሥርዓቱን ማዘመንና የወጪ ንግድን ማሳደግን በተመለከተም ዘርፈ ብዙ ሥራዎች መከናወናቸውን ያነሱት ሚኒስትሩ፤ እነዚህ ስኬቶች ሀገሪቱ በበጀት ዓመቱ ከወጪ ንግድ ለማግኘት ያቀደችውን የ10 ነጥብ 7 ቢሊየን ዶላር ገቢ ግብ ለማሳካት የሚያስችሉና ትልቅ አቅም የፈጠሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በተጨማሪም ዘመናዊ የግብይት ማዕከላትን በማስፋፋት በኩል አበረታች ሥራዎች መከናወናቸውንና በአሁኑ ወቅት የማዕከላቱ ቁጥር ከ31 በላይ መድረሱን ተናግረዋል።

ከዚሁ ጋር ተያይዞም የ10 ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት የግብይት ማዕከላት ግንባታ የተጀመረ ሲሆን፣ ሁለቱ ተጠናቀው በበጀት ዓመቱ ለአገልግሎት ክፍት መደረጋቸውን አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026