የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የሀገሪቱን የዲጂታላይዜሽን ጉዞ ለማፋጠን አካባቢዎችን ወደ ዲጂታል አድራሻ ሥርዓት የማስገባት ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል

Jul 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ የሀገሪቱን የዲጂታላይዜሽን ጉዞ ለማፋጠን የተለያዩ አካባቢዎችን ወደ ዲጂታል አድራሻ ሥርዓት የማስገባት ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት አስታወቀ።

ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት የሀገሪቱን ሁለንተናዊ ምጣኔ ሀብታዊ እና ልማታዊ ዕድገት እንዲሁም የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025/2030” ስትራቴጂን ቀጣይነት ባለው መንገድ ተግባራዊ በማድረግ ላይ ትገኛለች።

የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ በላቸው ፀሐይ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ሀገሪቱ ወደ ዲጂታላይዜሽን እንዲሁም ወደ ስማርት ሲቲነት ለመቀየር በከፍተኛ ግስጋሴ ላይ የምትገኝ መሆኗን ገልጸዋል።

መንግሥት ለዲጂታላይዜሽን ጉዞ መሠረት የሆኑ ዘርፈ ብዙ የመሠረተ ልማት ማስፋፊያ ሥራዎችን ያከናወነ ሲሆን፣ ዜጎች ከቴክኖሎጂው ጋር አብረው መራመድ የሚችሉበትን ዕውቀትና ክህሎት እንዲያገኙ በርካታ ጥረቶች እየተደረጉ ይገኛሉ ብለዋል፡፡

ለአብነትም የኢትዮ-ኮደርስ አምስት ሚሊዮን ዜጎች ስልጠና ሰፊ መድረክ መመቻቸቱን ጠቅሰው ለጀማሪ ሥራ ፈጣሪዎች አዳዲስ የፈጠራ ሥራዎች የሚደገፉበት ምቹ መደላድል መፈጠሩን ጠቅሰዋል፡፡

የተለያዩ ተቋማት የቴክኖሎጂ አጠቃቀማቸውን በማስፋት የመንግሥት አገልግሎቶችን፣ የንግድ ሥርዓቶችን እና የዜጎችን የዕለት ተዕለት ኑሮ እንዲያዘምኑ መንገድ መከፈቱንም ጠቁመዋል፡፡

የዲጂታል አድራሻ ሥርዓት መዘርጋት ሀገሪቱ ወደ ስማርት ከተማነት ለምታደርገው ግስጋሴ ስኬት ወሳኝ በመሆኑ፤ ኢንስቲትዩቱ በትኩረት ሲሠራበት መቆየቱን ጠቅሰዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት በአጠቃላይ ወደ 40 የሚጠጉ አከባቢዎች ወደ ዲጂታል አድራሻ ሥርዓት ማስገባት የሚያስችሉ ተግባራት በመከናወን ላይ እንደሚገኙ ጠቁመዋል፡፡

እስከ 2018 ዓ.ም ድረስ በሀገሪቱ የሚገኙ ዘጠኝ ከተሞችን ወደ ዲጂታል አድራሻ ለማስገባት የሚያስችሉ መረጃዎች መሰብሰባቸውን ጠቅሰው፤ ከእነዚህም ውስጥ በተለያዩ ከተሞች የተገነቡ የዲጂታል አድራሻ ሥርዓቶች ቀድመው ወደ አገልግሎት ገብተዋል።

የዲጂታል አድራሻ ሥርዓት መዘርጋቱ ዜጎች በቴክኖሎጂ የተደገፉና ዘመኑን የዋጁ መረጃዎችን በቀላሉ እንዲያገኙ ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል።

በመሆኑም የዲጂታላይዜሽን ጉዞ ይበልጥ ለማፋጠን፣ የተለያዩ አካባቢዎችን ወደዚህ ዘመናዊ አድራሻ ሥርዓት የማስገባቱ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026