የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የሀገሪቱን የዲጂታላይዜሽን ጉዞ ለማፋጠን አካባቢዎችን ወደ ዲጂታል አድራሻ ሥርዓት የማስገባት ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል

Jul 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ የሀገሪቱን የዲጂታላይዜሽን ጉዞ ለማፋጠን የተለያዩ አካባቢዎችን ወደ ዲጂታል አድራሻ ሥርዓት የማስገባት ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት አስታወቀ።

ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት የሀገሪቱን ሁለንተናዊ ምጣኔ ሀብታዊ እና ልማታዊ ዕድገት እንዲሁም የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025/2030” ስትራቴጂን ቀጣይነት ባለው መንገድ ተግባራዊ በማድረግ ላይ ትገኛለች።

የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ በላቸው ፀሐይ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ሀገሪቱ ወደ ዲጂታላይዜሽን እንዲሁም ወደ ስማርት ሲቲነት ለመቀየር በከፍተኛ ግስጋሴ ላይ የምትገኝ መሆኗን ገልጸዋል።

መንግሥት ለዲጂታላይዜሽን ጉዞ መሠረት የሆኑ ዘርፈ ብዙ የመሠረተ ልማት ማስፋፊያ ሥራዎችን ያከናወነ ሲሆን፣ ዜጎች ከቴክኖሎጂው ጋር አብረው መራመድ የሚችሉበትን ዕውቀትና ክህሎት እንዲያገኙ በርካታ ጥረቶች እየተደረጉ ይገኛሉ ብለዋል፡፡

ለአብነትም የኢትዮ-ኮደርስ አምስት ሚሊዮን ዜጎች ስልጠና ሰፊ መድረክ መመቻቸቱን ጠቅሰው ለጀማሪ ሥራ ፈጣሪዎች አዳዲስ የፈጠራ ሥራዎች የሚደገፉበት ምቹ መደላድል መፈጠሩን ጠቅሰዋል፡፡

የተለያዩ ተቋማት የቴክኖሎጂ አጠቃቀማቸውን በማስፋት የመንግሥት አገልግሎቶችን፣ የንግድ ሥርዓቶችን እና የዜጎችን የዕለት ተዕለት ኑሮ እንዲያዘምኑ መንገድ መከፈቱንም ጠቁመዋል፡፡

የዲጂታል አድራሻ ሥርዓት መዘርጋት ሀገሪቱ ወደ ስማርት ከተማነት ለምታደርገው ግስጋሴ ስኬት ወሳኝ በመሆኑ፤ ኢንስቲትዩቱ በትኩረት ሲሠራበት መቆየቱን ጠቅሰዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት በአጠቃላይ ወደ 40 የሚጠጉ አከባቢዎች ወደ ዲጂታል አድራሻ ሥርዓት ማስገባት የሚያስችሉ ተግባራት በመከናወን ላይ እንደሚገኙ ጠቁመዋል፡፡

እስከ 2018 ዓ.ም ድረስ በሀገሪቱ የሚገኙ ዘጠኝ ከተሞችን ወደ ዲጂታል አድራሻ ለማስገባት የሚያስችሉ መረጃዎች መሰብሰባቸውን ጠቅሰው፤ ከእነዚህም ውስጥ በተለያዩ ከተሞች የተገነቡ የዲጂታል አድራሻ ሥርዓቶች ቀድመው ወደ አገልግሎት ገብተዋል።

የዲጂታል አድራሻ ሥርዓት መዘርጋቱ ዜጎች በቴክኖሎጂ የተደገፉና ዘመኑን የዋጁ መረጃዎችን በቀላሉ እንዲያገኙ ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል።

በመሆኑም የዲጂታላይዜሽን ጉዞ ይበልጥ ለማፋጠን፣ የተለያዩ አካባቢዎችን ወደዚህ ዘመናዊ አድራሻ ሥርዓት የማስገባቱ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026